Category Archives: Wisdom
የእውቀት ችግር የእግዚአብሔር ችግር ነው
ሰው እውቀት ያስፈልገዋል፡፡ መፅሃፍ ቅዱስ ነፍስ ያለእውቀት ትሆን ዘንድ መልካም አይደለም ይላል፡፡ ሰው እውቀት ከጎደለውቅ ሁሉ ነገር ይጎድለዋል፡፡
ነፍስ እውቀት የሌለባት ትሆን ዘንድ መልካም አይደለም፤ እግሩንም የሚያፈጥን ከመንገድ ይስታል። መጽሐፈ ምሳሌ 19፡2
ሰው በእግዚአብሄር የተፈጠረው በእግዚአብሄር መልክና አምሳል ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው ከሚያስፈልገው ከሙሉ እውቀት ጋር ነው፡፡ ሰው ለኑሮ የሚያስፈልገው እውቀት ሁሉ ነበረው፡፡ ሰው እግዚአብሄርን በሚገባ ያውቀው ነበር፡፡ ሰው ስለ እግዚአብሄር የሚያስፈልገው እውቀት ሁሉ ነበረው፡፡
ሰው በሰይጣን ማታለል ምክንያት የማያስፈልገውን እውቀት ሲፈልግል ለኑሮና ለስኬት የሚያስፈልገውን ዋናውን እውቀት አጣው፡፡ ሰው የእግዚአብሄርን እውቀት ሲያጣው ስለሌላ ስለሁሉም ነገሮች ያሉት እውቀቶች ሁሉ ተዛቡበት፡፡ ሰው ስለ እግዚአብሄር ያለውን ትክክለኛውን እውቀት ሲያጣው ስለራሱ ያለውን ትክክለኛ እውቀት አጣው፡፡ ሰው ስለ እግዚአብሄር ያለውን ትክክለኛ እውቀት ሲያጣው በእግዚአብሄር መልክና አምሳል ስለተፈጠረው ሰው ትክክለኛውንና ንፁህን እውቀት አጣው፡፡
ነገር ግን እባብ በተንኮሉ ሔዋንን እንዳሳታት፥ አሳባችሁ ተበላሽቶ ለክርስቶስ ከሚሆን ቅንነትና ንጽሕና ምናልባት እንዳይለወጥ ብዬ እፈራለሁ። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 11፡3
የሰው የእውቀት ችግር የተጀመረው ከእግዚአብሄር ነው፡፡ ሰው ለእግዚአብሄር ያለው እውቀት ሲዛባ ሌላ ሁሉ እውቀቱ ተዛባ፡፡
ሰው እውቀት ካስፈለገው መጀመሪያ ማወቅ ያለበት የእግዚአብሄርን እውቀት ነው፡፡ ሰው ወደ እውቀት ከተመለሰ መመለስ ያለበት ወደ እግዚአብሄር እውቀት ነው፡፡ ሰው እውቀት ካስፈለገው እውቀትን መጀመር ያለበት እንዴት ከእግዚአብሄር ጋር እንደሚኖር በማወቅ ነው፡፡
ሰው እውቀት አለኝ የሚለው መጀመሪያ ከፈጠረው ከእግዚአብሄር ጋር እንዴት እንደሚኖር በማወቅ ነው፡፡ ሰው እውቀት አለኝ ማለት የሚችለው ለእግዚአብሄር አምላክነት እውቅና በመስጠት ነው፡፡ ሰው እውቀት አለኝ ማለት የሚችለው እግዚአብሄርን በመፍራት ነው፡፡
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ሰነፎች ግን ጥበብንና ተግሣጽን ይንቃሉ። መጽሐፈ ምሳሌ 1፡7
የሰው እውነተኛ እውቀት የሚጀምረው በመልኩና በአምሳሉ የፈጠረውን እግዚአብሄርን እንደ አምላክነቱ አውቅና በመስጠት ነው፡፡
ስለዚህም እግዚአብሔርን እያወቁ እንደ እግዚአብሔርነቱ መጠን ስላላከበሩትና ስላላመሰገኑት የሚያመካኙት አጡ፤ ነገር ግን በአሳባቸው ከንቱ ሆኑ የማያስተውለውም ልባቸው ጨለመ። ወደ ሮሜ ሰዎች 1፡20-21
ሰው ከፈጣሪው ጋር እንደት በትህትና እንደሚሄድ ካላወቅ ሌላው እውቀቱ ሁሉ ከንቱ ነው፡፡
ሰው ሆይ፥ መልካሙን ነግሮሃል፤ እግዚአብሔርም ከአንተ ዘንድ የሚሻው ምንድር ነው? ፍርድን ታደርግ ዘንድ፥ ምሕረትንም ትወድድ ዘንድ፥ ከአምላክህም ጋር በትሕትና ትሄድ ዘንድ አይደለምን? ትንቢተ ሚክያስ 6፡8
ሰው ከእግዚአብሄር ጋር እንዴት እንደሚኖር ካላወቀ ሌላ እውቀትን መሰብሰብ ራስብን ማድከም ነው፡፡
ከዚህም ሁሉ በላይ፥ ልጄ ሆይ፥ ተግሣጽን ስማ፤ ብዙ መጻሕፍትን ማድረግ ፍጻሜ የለውም፥ እጅግም ምርምር ሰውነትን ያደክማል። የነገሩን ሁሉ ፍጻሜ እንስማ፤ ይህ የሰው ሁለንተናው ነውና፤ እግዚአብሔርን ፍራ፥ ትእዛዙንም ጠብቅ። መጽሐፈ መክብብ 12፡12-13
ሰው እግዚአብሄርን የመፍራት ጥበብ ከሌለው ምንም ጥበብ እንደሌለው ይቆጠራል፡፡ ሰው እግዚአብሄርን የመፍራት ጥበብ ካለው ደግሞ ለኑሮ ለስኬትና ለክንውን የሚያስፈልገው ጥበብ ሁሉ እንዳለው ይቆጠራል፡፡
አሁን ያለው የሰው የእውቀት ችግር ሁሉ የእግዚአብሄር እውቀት ችግር ነው፡፡ የሰው የእውቀት ችግር ሁሉ የሚፈታው የእግዚአብሄር እውቀት ችግር ሲፈታ ነው፡፡ ስለዚህ ነው ህዝቤ አውቀት ከማጣት የተነሳ ጠፍቶዋል የሚለው፡፡
ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል፤ አንተም እውቀትን ጠልተሃልና እኔ ካህን እንዳትሆነኝ እጠላሃለሁ፤ የአምላክህንም ሕግ ረስተሃልና እኔ ደግሞ ልጆችህን እረሳለሁ። ትንቢተ ሆሴዕ 4፡6
ሰው የእውቀት ችግሩ የሚፈታው የእግዚአብሄርን እውነት ሲያውቅ በነው፡፡ ሰው ራሱንና ሌላውን ሰው በትክክል የሚያውቅው እግዚአብሄርን ሲያውቅ ነው፡፡ የሰው የእውቀት ችግር የሚፈታው የእግዚአብሄር እውቀት ችግር በህይወቱ ሲፈታ ብቻ ነው፡፡
እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል አላቸው። የዮሐንስ ወንጌል 8፡32
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #ሃሳብ #ጥበብ #ማስተዋል #እግዚአብሔርንመፍራት #ጥበብ #ክፉ #መልካም #ፍርድ #እውቅና #ፍፁም #ችግር #መፍትሄ #አላማ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #እምነት #ቃል #ማደስ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
በአእምሮ ሕፃናት አትሁኑ
በአእምሮ ሕፃናት አትሁኑ
ክፉን በክፉ ላለመመለስ ህፃናተ ሁኑ እንጂ ስለህይወታችሁ እወቁ፡፡ ህይወታችሁን እንዳመጣላችሁ አትምሩት፡፡ ህይወታቸሁን ለመምራት አስቡ አቅዱ በእግዚአብሄር ቃል የታደሰ አእምሮዋችሁን ተጠቀሙ፡፡
ወንድሞች ሆይ፥ በአእምሮ ሕፃናት አትሁኑ፤ ለክፋት ነገር ሕፃናት ሁኑ እንጂ በአእምሮ የበሰሉ ሁኑ። 1ኛ ቆሮንቶስ 14፡20
መውጫ መግቢያውን የምትቃኙ ንቁዎችና ብልሆች ሁኑ እንጂ ወደ ወሰዷችሁ የምትጎተቱ ሞኞች አትሁኑ፡፡
እነሆ፥ እኔ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል እልካችኋለሁ፤ ስለዚህ እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ። የማቴዎስ ወንጌል 10፡16
ነገር ግን እባብ በተንኮሉ ሔዋንን እንዳሳታት፥ አሳባችሁ ተበላሽቶ ለክርስቶስ ከሚሆን ቅንነትና ንጽሕና ምናልባት እንዳይለወጥ ብዬ እፈራለሁ። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 11፡3
በእእምሮው ህፃን የሆነ ሰው የራሱ የህይወት መርህ የለውም የመጣው ነገር ሁሉ ይወስደዋል፡፡
ልጅ ሳለሁ እንደ ልጅ እናገር ነበር፥ እንደ ልጅም አስብ ነበር፥ እንደ ልጅም እቈጥር ነበር፤ ጎልማሳ ሆኜ ግን የልጅነትን ጠባይ ሽሬአለሁ። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13፡11
እንደ ስሕተት ሽንገላ ባለ ተንኮል በሰዎችም ማታለል ምክንያት በትምህርት ነፋስ ሁሉ እየተፍገመገምን ወዲያና ወዲህም እየተንሳፈፍን ሕፃናት መሆን ወደ ፊት አይገባንም፥ ወደ ኤፌሶን ሰዎች 4፡14
በአእምሮው የበሰለ ሰው የሰው የግል መጠቀሚያ አይሆንም፡፡ በአእምሮ የበሰለ ሰው ዘሎ ውሳኔን አይወስንም በአእመሮ ህፃን ያልሆነ ሰው አካሄድን ይመለከታል ይመዝናል፡፡
በብርቱ ይፈልጉአችኋል፥ ለመልካም አይደለም ነገር ግን በብርቱ ትፈልጉአቸው ዘንድ በውጭ ሊያስቀሩአችሁ ይወዳሉ። ወደ ገላትያ ሰዎች 4፡17
የዋህ ቃልን ሁሉ ያምናል፤ ብልህ ግን አካሄዱን ይመለከታል። መጽሐፈ ምሳሌ 14፡15
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ልብ #ህፃንነት #ብስለት #ጥበብ #ማስተዋል #አላማ #መሰረታዊፍላጎት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ጥሪ #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #አንድነት #ትህትና #አክብሮት #ስልጣን #መሪ
በብዙም ሆነ በጥቂቱ ማዳን አይሳንህም
በብዙም ሆነ በጥቂቱ ማዳን አይሳንህም
ሰው ከምንም ነገር በላይ በሚያደርገው ነገር ሁሉ እግዚአብሄር አብሮት እንዳለ የሚያደርገው ነገር እግዚአብሄር ያለውን ነገር መሆኑን ማረጋገጥ አለበት፡፡
እግዚአብሔርም፦ እኔ ከአንተ ጋር እሄዳለሁ፥ አሳርፍህማለሁ አለው። እርሱም፦ አንተ ከእኛ ጋር ካልወጣህስ፥ ከዚህ አታውጣን። ኦሪት ዘጸአት 33፡14-15
ልዩነት የሚያመጣው የእኛ ብዛትና ማነስ አይደለም፡፡ ልዩነት የሚያመጣው የእኛ መበርታትና መድከም አይደለም፡፡ ልዩነት የሚያመጣው የእኛ አዋቂነትና አላዋቂነት አይደለም፡፡ ልዩነት የሚያመጣው የእኛ ዝናና አለመታወቅ አይደለም፡፡ ልዩነት የሚያመጣው እግዚአብሄር ነው፡፡ ልዩነት የሚያመጣው እግዚአብሄር ከእኛ ጋር መሆኑ ነው፡፡ እግዚአብሄር ደግሞ ሁሉን ቻይ አምላክ ነው፡፡ እግዚአብሄር ደግሞ የሚሳነው ነገር የለም፡፡ እግዚአብሄር ደግሞ በብዙም ሆነ በጥቂቱ ማዳን አያቅተውም፡፡
አሳም፦ አቤቱ፥ በብዙም ሆነ በጥቂቱ ማዳን አይሳንህም፤ አቤቱ አምላካችን ሆይ፥ በአንተ ታምነናልና፥ በስምህም በዚህ ታላቅ ወገን ላይ መጥተናልና እርዳን፤ አቤቱ፥ አምላካችን አንተ ነህ፤ ሰውም አያሸንፍህ ብሎ ወደ አምላኩ ወደ እግዚአብሔር ጮኸ። መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 14፡11
ወይም ልዩነት የሚያመጣው ምቹ ስፍራ መሆንህና አለመሆንህ አይደለም፡፡ የእስራኤል ህዝብን እግዚአብሄር ከምድረበዳ ስጋን እንዴት ሊያመጣ ይችላል ብለው አሙት፡፡ እግዚአብሄር በጊዜና በቦታ አይወሰንም፡፡ እግዚአብሄር ግን ጊዜና ቦታ አይገድበውም፡፡ ለእግዚአብሄር ግን የሚሳነው ነገር የለም፡፡
ለነፍሳቸው መብልን ይፈልጉ ዘንድ፥ እግዚአብሔርን በልባቸው ፈተኑት። እግዚአብሔርን እንዲህ ብለው አሙት፦ እግዚአብሔር በምድረ በዳ ማዕድን ያሰናዳ ዘንድ ይችላልን? ዓለቱን መታ፤ ውኆችም ወጡ፥ ወንዞችም ጐረፉ፤ እንጀራን መስጠትስ ይችላልን? ለሕዝቡስ ማዕድን ያዘጋጃልን? መዝሙረ ዳዊት 78፡18-20
እግዚአብሄር በሰው ነገር አይታመንም፡፡ እግዚአብሄር በሰው ችሎታ አይደገፈም፡፡ እግዚአብሄር የራሱ ክንድ መድሃኒት ታመጣለታለች፡፡
ሰውም እንደሌለ አየ፥ ወደ እርሱ የሚማልድ እንደሌለ ተረዳ ተደነቀም፤ ስለዚህ የገዛ ክንዱ መድኃኒት አመጣለት፥ ጽድቁም አገዘው። ትንቢተ ኢሳይያስ 59፡16
ተመለከትሁ፥ የሚረዳም አልተገኘም፤ የሚያግዝም አልነበረምና ተደነቅሁ፤ ስለዚህ የገዛ ክንዴ መድኃኒት አመጣልኝ፥ ቍጣዬም እርሱ አገዘኝ። ትንቢተ ኢሳይያስ 63፡5
በብዙ ወይም በጥቂት ማዳን እግዚአብሔርን አያስቸግረውምና፡፡ ሰው እግዚአብሄር የፈለገበትን ነገር እንደሚሰራ ካወቀ ስለብዛት መጨነቅ የለበትም፡፡ እግዚአብሄር ደጋፊ ቲፎዞ አይፈልግም፡፡ እግዚአብሄር በሰው በብዛት አይደገፍም፡፡
ዮናታንም ጋሻ ጃግሬውን፦ ና፥ ወደ እነዚህ ቈላፋን ጭፍራ እንለፍ፤ በብዙ ወይም በጥቂት ማዳን እግዚአብሔርን አያስቸግረውምና ምናልባት እግዚአብሔር ይሠራልን ይሆናል አለው። መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 14፡6
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ትህትና #አይሳነውም #ባለቤት #ዝቅታ #ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #አዋቂ #በጥቂት #በብዙ #ማዳን #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ተስፋ #ፍቅር #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ
ለሰይጣን ሽንገላ ፍቱን መድሃኒቱ
ሰይጣን በትእቢት ምክንያት ከመውደቁ በፊት የእግዚአብሄር አገልጋይ ነበር፡፡ ሰይጣን የእግዚአብሄርን ቦታ ፈልጎ ከመዋረዱ በፊት በእግዚአብሄር ጥበብ ይኖር ነበር፡፡ ሰይጣን በሃጢያት ምክንያት ሲወድቅ ነው ጥበብህን አረከስህ የተባለው፡፡
በውበትህ ምክንያት ልብህ ኰርቶአል፤ ከክብርህ የተነሣ ጥበብህን አረከስህ፤ በምድር ላይ ጣልሁህ ያዩህም ዘንድ በነገሥታት ፊት ሰጠሁህ። ሕዝቅኤል 28፡17
ሰይጣን የረከሰ ጥበብ ይሁን እንጂ አሁንም ጥበብ አለው፡፡ ሰይጣን ይዋሻል፡፡ ሰይጣን ሰዎችን ያሳምናል፡፡ ሰይጣን ሰዎችን ያታልላል፡፡ ሰይጣን በረከሰው ጥበብ ተጠቅሞ ሰዎችን ያስታል፡፡ ሰይጣን ጥበቡን ተጠቅሞ ሰዎችን በእግዚአብሄር ላይ ያሳምፃል፡፡ ሰይጣን ጥበቡን ተጠቅሞ የሰዎችን ህይወት ያጠፋል ያበላሻል፡፡
ሰይጣን ሰዎችን በማታለል ይሰርቃል ያርዳል ያጠፋል፡፡
ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ። ዮሃንስ 10፡10
ሰይጣን ይዋሻል፡፡ ሰይጣን ሰዎችን ያስታል፡፡ ሰይጣን ሄዋንን አስቶዋታል፡፡ ሰይጣን በእግዚአብሄር ጥበብ በቀጣይነት የማይኖረውን ማንኛውንም ሰው ሊያስት ይችላል፡፡
እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ። እርሱ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ፤ እውነትም በእርሱ ስለ ሌለ በእውነት አልቆመም። ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል፥ ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና። ዮሃንስ 8፡44
ሰይጣን አያታልለንም ብለን በከንቱ ብንፎክር ከሰይጣን ማታለል አናመልጥም፡፡ ሰይጣን የራሱ የማታለል ሃይለ አለው፡፡ ሰይጣን ምንም አያመጣም ብለን ብንኩራራ ራሳችን ምንም አናመጣም፡፡
የረከሰ ጥበብ ይሁን እንጂ ሰይጣን የራሱ ጥበብ ስላለው ካለ እግዚአብሄር ጥበብ በስተቀር ከሰይጣን ማታለል ማምለጥ አንችልም፡፡ በሰይጣን ላለመሳት ከፈለግን የእግዚአብሄር ጥበብ ያስፈልገናል፡፡ የሰይጣንን ሽንገላ የምንቃወምበት የእግዚአብሄርን ጥበብ ማንሳይ አለብን፡፡ ካለ እግዚአብሄር ጥበብ የሰይጣንን ሽንገላ መቃወም አንችልም፡፡
ካለ እግዚአብሄር ጥበብ የሰይጣንን ሽንገላ የምንቃወም ከመሰለን በራሱ በሰይጣን ተታልለናል ማለት ነው፡፡ በሰይጣን ላለመበለጥ የሰይጣንን ማታለል የሚበልጥ ጥበብ ያስፈልገናል፡፡ የምንበረታው በራሳችን ሃይል ሳይሆን በጌታ ሃይል ብቻ ነው፡፡
በቀረውስ በጌታና በኃይሉ ችሎት የበረታችሁ ሁኑ። የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ። ኤፌሶን 6፡10-11
ከእግዚአብሄር ብቻ በምናገኘው ዘርፈ ብዙ ጥበብ በመታገዝ ብቻ ነው የሰይጣንን ሽንገላ እያለ በእኛ ላይ ምንም ሃይል እንዳይኖረው ማድረግ የምንችለው፡፡ በአለቆችና ስልጣናት ላይ በሃይል የምንገለጠው በእግዚአብሄር ጥበብ ስንንቀሳቀስ ብቻ ነው፡፡
ብዙ ልዩ ልዩ የእግዚአብሔር ጥበብ አሁን በቤተ ክርስቲያን በኩል በሰማያዊ ስፍራ ውስጥ ላሉት አለቆችና ሥልጣናት ትታወቅ ዘንድ፤ ኤፌሶን 3፡10
በእግዚአብሄር ቃል ጥበብ ስንኖር ግን ኢየሱስ እንዳለው ሰይጣን በእኔ ላይ አንዳች የለውም ማለት እንችላለን፡፡
ከእንግዲህ ወዲህ ከእናንተ ጋር ብዙ አልናገርም፥ የዚህ ዓለም ገዥ ይመጣልና፤ በእኔ ላይም አንዳች የለውም፤ ዮሃንስ 14፡30
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ጥበብ #ማስተዋል #ሽንገላ #አለቆች #ስልጣናት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰይጣን #ዲያብሎስ #እምነት #ፈተና #ፀሎት #ጌታ #የእግዚአብሄርቃል #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
እምነታችሁም በሰው ጥበብ እንዳይሆን
እምነታችሁም በእግዚአብሔር ኃይል እንጂ በሰው ጥበብ እንዳይሆን፥ ቃሌም ስብከቴም መንፈስንና ኃይልን በመግለጥ ነበረ እንጂ፥ በሚያባብል በጥበብ ቃል አልነበረም። 1ኛ ቆሮንቶስ 2፡4-5
መንፈሳዊውን ነገር ከመንፈሳዊው ነገር ጋር አስተያይተን መንፈስ በሚያስተምረን ቃል ይህን ደግሞ እንናገራለን እንጂ የሰው ጥበብ በሚያስተምረን ቃል አይደለም። 1ኛ ቆሮንቶስ 2፡13
ጥበብ ስለተባለ ብቻ ጥበብ ሁሉ አንድ አይደለም፡፡ በምድር ላይ የሰው ጥበብ አለ የእግዚአብሄር ጥበብ ደግሞ አለ፡፡ የሰው ጥብብና የእግዚአብሄር ጥብብ እጅግ የተለያዩ ጥበቦች ናቸው፡፡
የእግዚአብሄርና የሰው ጥበብ በሚያፈሩዋቸው ፍሬዎች ይታወቃሉ፡፡
ከእናንተ ጥበበኛና አስተዋይ ማን ነው? በመልካም አንዋዋሩ ስራውን በጥበብ የዋህነት ያሳይ። ያዕቆብ 3፡13
ከእግዚአብሄር ዘንድ የሆነው ጥበብ ንፁህ ፥ ታራቂ፥ ገር፥ እሺ ባይ ምሕረትና በጎ ፍሬ የሞላባት ፣ ጥርጥርና ግብዝነት የሌለበት ነው፡፡
ላይኛይቱ ጥበብ ግን በመጀመሪያ ንጽሕት ናት፥ በኋላም ታራቂ፥ ገር፥ እሺ ባይ ምሕረትና በጎ ፍሬ የሞላባት፥ ጥርጥርና ግብዝነት የሌለባት ናት። ያዕቆብ 3፡17
የሰው የሆነው ጥበብ መራርነት ቅንአትንና አድመኝነትን ያፈራል፡፡
ነገር ግን መራራ ቅንዓትና አድመኛነት በልባችሁ ቢኖርባችሁ፥ አትመኩ በእውነትም ላይ አትዋሹ። ይህ ጥበብ ከላይ የሚወርድ አይደለም፤ ነገር ግን የምድር ነው፥ የሥጋም ነው፥ የአጋንንትም ነው፤ ቅንዓትና አድመኛነት ባሉበት ስፍራ በዚያ ሁከትና ክፉ ስራ ሁሉ አሉና። ያዕቆብ 3፡14-16
ከሚሰበኩት ስብከት የተነሳ እምነታቸው በሰው ጥበብ ላይ የሚሆን ሰዎች አሉ፡፡ ከሚሰበኩት ስብከት የተነሳ ደግሞ እምነታቸው በእግዚአብሄር ሃይል ላይ የሚሆን ሰዎች አሉ፡፡ በሚያባብል በጥበብ ቃል የሚሰበኩ ሰዎች አሉ፡፡ የእግዚአብሄርን መንፈስ በመግለጥ የሚሰበኩ ሰዎች አሉ፡፡ የሚያባብል በጥበብ ቃል የተሰበከ ሰው እምነቱ በሰው ጥበብ ላይ ነው የሚሆነው፡፡ የእግዚአብሄርን መንፈስ በመግለጥ የሚሰበኩ ሰዎች እምነታቸው የሚሆነው በእግዚአብሄር ሃይል ላይ ነው፡፡
እምነታችሁም በእግዚአብሔር ኃይል እንጂ በሰው ጥበብ እንዳይሆን፥ ቃሌም ስብከቴም መንፈስንና ኃይልን በመግለጥ ነበረ እንጂ፥ በሚያባብል በጥበብ ቃል አልነበረም። 1ኛ ቆሮንቶስ 2፡4-5
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ጥበብ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ማስተዋል #እምነት #የሰውጥበብ #የእግዚአብሄርጥበብ #በሚያባብል #ተንኮል #መራራ #ቅንዓትና #አድመኛነት #የእግዚአብሄርቃል #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
ሰነፎች ግን ጥበብንና ተግሣጽን ይንቃሉ
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ሰነፎች ግን ጥበብንና ተግሣጽን ይንቃሉ። ምሳሌ 1፡7
ነፍስ ያለእውቀት ትሆን ዘንድ መልካም አይደለም፡፡ ጥበብና እውቀት ከሚገኝበት መንገድ አንዱ ተግሳፅ ነው፡፡ ተግሳፅ የሰው ሃብት ነው፡፡ ተግሳፅን የሚሰማ ሰው ደግሞ ተግሳፅ ከክፉ ይጠብቀዋል፡፡
ተግሳፅን የማይሰማ ሰው ግን ያንኑ ስንፍና ሲደግመው ሳያድግና ሳይለወጥ እንደተፀፀተ ይኖራል፡፡ ሰነፍ ሰው በተግሳፅ ለመታረም ከመትጋተ ይልቅ ስንፍናው በህይወት ከፍተኛ ዋጋ እንዲከፍል ያደርገዋል፡፡
እውነትን ግዛ አትሽጣትም፥ ጥበብን ተግሣጽን ማስተዋልንም። ምሳሌ 23፡23
ሰው ስለዘለፋ እና ተግሳፅ ጥቅም እውቀት ከሌለው ዘለፋንና ተግሳፅን ይንቃል፡፡ ዘለፋና ተግሳፅ ያላቸውን ዋጋ የተረዳ ሰው ያከብራቸዋል፡፡ የተግሳፅን አስፈላጊነት የተረዳ ሰው ለተግሳፅ ሙሉ ልቡን ይሰጣል፡፡ የዘለፋን ጥቅም ያወቀ ሰው የዘለፋን ጥቅም ሙሉ ለሙሉ እስከሚጠቀምበት ድረስ ዘለፋን አያልፈውም፡፡
ተግሣጽን ያዝ፥ አትተውም፤ ጠብቀው፥ እርሱ ሕይወትህ ነውና።ምሳሌ 4፡13
የዘለፋን ጥቅም የማያውቅ ሰው ግን የገሰፀው ሰው ጠላቱ ይመስለዋል፡፡ የተግሳፅን አስፈላጊነት ያልተረዳ ሰው ግን የሚገስፀው ሰው ያለአግባብ የሚጠቀምበት ይመስለዋል፡፡
በእግራቸው እንዳይረግጡት ተመልሰውም እንዳይነክሱአችሁ፥ የተቀደሰውን ለውሾች አትስጡ፥ ዕንቁዎቻችሁንም በእሪያዎች ፊት አትጣሉ። ማቴዎስ 7፡6
ሰው ከተግሳፅ ምን እጠቀማለሁ ማለቱ ግን ወሳኝ ነው፡፡ ተግሳፅ ራሳችንን እንድናይ ያደርገናል፡፡ ተግሳፅ እኔ ሃላፊነት የመወስደው ስለየቱ ጥፋት ነው ብለን ራሳችንን እንድንጠይቅ ያደርገናል፡፡ ተግሳፅ ራሳችንን እንድናነፃ እድልን ይሰጠናል፡፡ ተግሳፅ ትክክል ብንሆን እንኳን ትክክል መሆናችንን ያፀናልናል፡፡
ብልህ ሰው ህይወት ከሚገስፀው ሰው ቢገስፀው ይሻለዋል፡፡ ብልህ ሰው ውድቀት ከሚያዋርደው ዘለፋ ቢያዋርደው ይቀለዋል፡፡ ጠቢብ ሰው መከራ ከሚመክረው ሰው ቢመክረው ይሻለዋል፡፡
ዘለፋን የሚጠላ ገንዘቡ የማያደርግ ሰው ዘለፋን የሚንቅ ቸልተኛ ሰው በፍፃሜው እንዴት እንደሚፀፀት መፅሃፍ ቅዱስ ያስተምራል፡፡ አትናገሩኝ የሚል ሰው በትእቢቱ ይፀፀታል፡፡
በመጨረሻም ሥጋህና ሰውነትህ በጠፋ ጊዜ ታለቅሳለህ፥ ትላለህም፦ እንዴት ትምህርትን ጠላሁ፥ ልቤም ዘለፋን ናቀ! የአስተማሪዎቼንም ቃል አልሰማሁም፥ ጆሮቼንም ወደ አስተማሪዎቼ አላዘነበልሁም። ምሳሌ 5፡11-13
ዘለፋን የሚታገስ ፡ በተግሳፅ ራሱን የሚያይ በተግሳፅ ተጠቅሞ ራሱን የሚያሻሻል ሰው እየለመለመ ፣ እያበበና እያፈራ ይቀጥላል፡፡
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #ሃሳብ #ጥበብ #ማስተዋል #ተግሳፅ #ዘለፋ #ጥበብ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #እምነት #ቃል #ማደስ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
ከክብርህ የተነሣ ጥበብህን አረከስህ
በውበትህ ምክንያት ልብህ ኰርቶአል፤ ከክብርህ የተነሣ ጥበብህን አረከስህ፤ በምድር ላይ ጣልሁህ ያዩህም ዘንድ በነገሥታት ፊት ሰጠሁህ። ሕዝቅኤል 28፡17
ሰይጣን እግዚአብሄር ላይ በማመፅ ከመውደቁ በፊት በእግዚአብሄር ጥበብ ነበር የሚኖረው፡፡ ሰይጣን ከክብሩ ሲወድቅ ግን የሰይጣን ጥበብ ረከሰ፡፡
ብዙ ጊዜ ብዙ ሰዎች የሚታለሉት ጥበበኛ የሆኑ እየመሰላቸው ነው፡፡ ጥበበሦች የሆኑ ሲመስላቸው የማያስተውሉ ይሆናሉ፡፡
ጥበበኞች ነን ሲሉ ደንቆሮ ሆኑ፥ ሮሜ 1፡22
ሰዎች ጥበብ አለን ይላሉ ነገር ግን ያላቸው ጥበብ ምን አይነት ጥበብ እንደሆነ አያስተውሉም፡፡ ሰዎች በጥበብ እየኖሩ ይመስላቸዋል ነገር ግን ያላቸውን የጥበብ አይነት ለይተው አያውቁትም፡፡
ሰዎች በአግዚአብሄር ጥበብ እየኖሩ እየመሰላቸው በሰይጣን ጥበብ ይኖራሉ፡፡
መፅሃፍ ቅዱስ ጥበብ ሁሉ እውነተኛ ጥበብ እንዳይደለ ያስተምራል፡፡ ጥበብ ሁሉ ንፁህ ጥበብ እንዳይደለ መፅሃፍ ቅዱስ ያስተምራል፡፡ ንፁህ ጥበብ እንዳለ ሁሉ የረከሰ ጥብብ እንዳለ መፅሃፍ ቅዱስ በግልፅ ያስተምረናል፡፡
ሰይጣን ጥበብ አለው፡፡ ነገር ግን የሰይጣን ጥበብና የእግዚአብሄር ጥበብ አንድ አይደሉም፡፡ የሰይጣን ጥበብ የረከሰ ጥበብ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ጥብብ ቅዱስ ጥበብ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ጥበብ የየዋህነት ጥበብ ነው፡፡ የሰይጣን ጥበብ የተንኮል ጥበብ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ጥበብ የይቅርታ ጥበብ ነው፡፡ የሰይጣን ጥበብ የመራርነት ጥበብ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ጥበብ የፍቅር ጥበብ ነው፡፡ የሰይጣን ጥበብ የቅንአት ጥበብ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ጥበብ የአንደነት ጥበብ ነው፡፡ የሰይጣን ጥበብ የአድመኝነትና የመከፋፈል ጥበብ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ጥበብ የሰላም ጥበብ ነው፡፡ የሰይጣን ጥበብ የጥል ጥበብ ነው፡፡
ከእናንተ ጥበበኛና አስተዋይ ማን ነው? በመልካም አንዋዋሩ ስራውን በጥበብ የዋህነት ያሳይ። ነገር ግን መራራ ቅንዓትና አድመኛነት በልባችሁ ቢኖርባችሁ፥ አትመኩ በእውነትም ላይ አትዋሹ። ይህ ጥበብ ከላይ የሚወርድ አይደለም፤ ነገር ግን የምድር ነው፥ የሥጋም ነው፥ የአጋንንትም ነው፤ ቅንዓትና አድመኛነት ባሉበት ስፍራ በዚያ ሁከትና ክፉ ስራ ሁሉ አሉና። ላይኛይቱ ጥበብ ግን በመጀመሪያ ንጽሕት ናት፥ በኋላም ታራቂ፥ ገር፥ እሺ ባይ ምሕረትና በጎ ፍሬ የሞላባት፥ ጥርጥርና ግብዝነት የሌለባት ናት። ያዕቆብ 3፡13-17
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ጥበብ #ቤተክርስትያን #መራራ #ቅንዓትና #አድመኛነት #ንጽሕት #በኋላም #ታራቂ #ገር #እሺባይ #ጥርጥር #ግብዝነት ##አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ማስተዋል #እምነት #ፈተና #ፀሎት #ጌታ #የእግዚአብሄርቃል #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
እግዚአብሔር በእኛ ላይ አይደለም ፣ እግዚአብሔር ለእኛ ነው
እግዚአብሄር ቸር አምላክ ነው፡፡ እግዚአብሄር የማንንም እድገት አይጠላም፡፡ እግዚአብሄር የማንንም ደስታ አይቃወምም፡፡ እግዚአብሄር የነጻነት አምላክ ነው፡፡ እግዚአብሄር በእኛ ላይ አይደለም፡፡ እግዚአብሄር ለእኛ ነው፡፡
እግዚአብሄር የህግን ብዛት ዘርዝሮ ሰዎችን አሳስሮ የሚያስቀምጥ የስጋት አምላክ አይደለም፡፡
የእግዚአብሄር ትእዛዞች ከባዶች አይደሉም፡፡
ትእዛዛቱን ልንጠብቅ የእግዚአብሔር ፍቅር ይህ ነውና፤ ትእዛዛቱም ከባዶች አይደሉም። 1ኛ ዮሐንስ 5፡3
ሰው በነፃነት እንዲሰራ ፣ እንዲያድግና እንዲለወጥ እግዚአብሄር ይፈልጋል፡፡
እግዚአብሄር እጅግ ረቂቅ ከመሆኑ የተነሳ እግዚአብሄርን ለማስደሰት በስነመለኮት ዲግሪ ማግኘት ፣ ብዙ መፅሃፎችን ማንበብና ብዙ የምርምር ስራዎችን መስራት አይጠይቅም፡፡ እግዚአብሄርን ማስደሰት ሊደረስበት የማይቻል ውስብስብ ነገር አይደለም፡፡
ሰው እግዚአብሄር የሚፈልገውን ይህን አንድ ነገር ካደረገ ባለው እውቀት ተጠቅሞ እግዚአብሄርን ማስደሰት ይችላል፡፡
እግዚአብሄር አንድ የሚጠይቀው ነገር ግን አለ፡፡ ሰው ሌላ ምንም ነገር ባያደርግ ይህንን ነገር ግን እንዲያደርግ እግዚአብሄር ይጠብቃል፡፡
የትእዛዛት መደምደሚያ ይህ ነው፡፡ የትእዛዛት ሁሉ አላመ ሰው እግዚአብሄን በመፍራተ እንዲኖር ነው፡፡ የሰው ሃላፊነቱ ሁሉ ይህ ነው፡፡ እግዚአብሄርን መፍራት ትእዛዙን መጠበቅ፡፡
የነገሩን ሁሉ ፍጻሜ እንስማ፤ ይህ የሰው ሁለንተናው ነውና፤ እግዚአብሔርን ፍራ፥ ትእዛዙንም ጠብቅ። እግዚአብሔር ሥራን ሁሉ የተሰወረውንም ነገር ሁሉ፥ መልካምም ቢሆን ክፉም ቢሆን፥ ወደ ፍርድ ያመጣዋልና። መክብብ 12፡13-14
ምክኒያቱም እግዚአብሄር የሰውን ስራ ሁሉ ወደፍርድ ያመጣዋል፡፡ እግዚአብሄር የተሰወረውን መልካምም ይሁን ክፉ ስራ ወደፍርድ ያመጣዋል፡፡
ሰው እግዚአብሄርን በመፍራት እስካደረገው ድረስ በነጻነት መኖር መስራት መውጣትና መግባት ይችላል፡፡ እግዚአብሄር ለእኛ ነው፡፡
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #ሃሳብ #ጥበብ #ማስተዋል #እግዚአብሔርንመፍራት #ጥበብ #ክፉ #መልካም #ፍርድ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #እምነት #ቃል #ማደስ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
ለሰውም እንዲታዩ ሥራቸውን ሁሉ ያደርጋሉ
ለሰውም እንዲታዩ ሥራቸውን ሁሉ ያደርጋሉ፤ ስለዚህ አሽንክታባቸውን ያሰፋሉ ዘርፉንም ያስረዝማሉ፥ ማቴዎስ 23፡5
ለሰዎች ትታዩ ዘንድ ምጽዋታችሁን በፊታቸው እንዳታደርጉ ተጠንቀቁ፤ ያለዚያ በሰማያት ባለው አባታችሁ ዘንድ ዋጋ የላችሁም። እንግዲህ ምጽዋት ስታደርግ፥ ግብዞች በሰው ዘንድ ሊከበሩ በምኩራብ በመንገድም እንደሚያደርጉ በፊትህ መለከት አታስነፋ፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል። ማቴዎስ 6፡1-2
ባሪያዎች ሆይ፥ በቅን ልብ ጌታን እየፈራችሁ እንጂ፥ ለሰው ደስ እንደምታሰኙ ለታይታ የምትገዙ ሳትሆኑ፥ በሥጋ ጌቶቻችሁ ለሆኑ በሁሉ ታዘዙ። ቆላስይስ 3፡22
ስትጸልዩም እንደ ግብዞች አትሁኑ፤ ለሰው ይታዩ ዘንድ በምኩራብና በመንገድ ማዕዘን ቆመው መጸለይን ይወዳሉና፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል። ማቴዎስ 6፡5
የእግዚአብሔርን ፈቃድ እንደሚያደርጉ እንደ ክርስቶስ ባሪያዎች እንጂ ለሰው ደስ እንደምታሰኙ ለታይታ የምትገዙ አትሁኑ። ኤፌሶን 6፡6
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#እምነት #ሃሳብ #መነሻሃሳብ #ልብ #ንፁህ #ፍቅር #ፉክክር #ቃል #ክብር #ለታይታ #የእግዚአብሔርቃል #ቃሉንመስማት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
Survival of the fittest
When I was in high school I was taught a Biology theory called the survival of the fittest. Here is the Wikipedia definition of Survival of the fittest copied for you.
“Survival of the fittest” is a phrase that originated from Darwinian evolutionary theory as a way of describing the mechanism of natural selection. The biological concept of fitness is defined as reproductive success. In Darwinian terms the phrase is best understood as “Survival of the form that will leave the most copies of itself in successive generations.”
In nature if you adapt the environment you can live longer, you can produce more offspring and you will dominate the earth and can continue by overcoming danger or hardship.
The purpose of this article isn’t to argue whether or not the theory is true or not. I know God created the heavens and the earth and I know that those who give due respect to the creator survive.
But when I always think about the fear of the Lord the survival of the fittest theory comes to my mind.
Furthermore, just as they did not think it worthwhile to retain the knowledge of God, so God gave them over to a depraved mind, so that they do what ought not to be done. Romans 1:28
For although they knew God, they neither glorified him as God nor gave thanks to him, but their thinking became futile and their foolish hearts were darkened. Romans 1:21
God created the heavens and the earth. To survive on earth you need at least a wisdom. To survive on earth you need the wisdom of the fear of God.
The fear of God is the beginning of wisdom. If you don’t have this minimum requirement, you don’t survive on earth. You may live but not really live. You may exist but not be living.
The fear of the Lord is the beginning of wisdom, and knowledge of the Holy One is understanding. Proverbs 9:10
We can’t survive on earth and in life not fearing the Lord and not giving due respect for the God who has created us all and sustains the earth.
The fear of the LORD adds length to life, but the years of the wicked are cut short. Proverbs 10:27
Those who fear the Lord will survive having the goodness of God by their side.
How abundant are the good things that you have stored up for those who fear you, that you bestow in the sight of all, on those who take refuge in you. Psalm 31:19
Those who fear God survive evil by being delivered By God’s angels.
The angel of the Lord encamps around those who fear him, and he delivers them. Psalm 34:7
Those who fear the Lord are highly blessed and their generation survives by becoming blessed as well.
Praise the LORD. Blessed is the man who fears the LORD, who finds great delight in his commands. His children will be mighty in the land; the generation of the upright will be blessed psalms 112:2
According to the Bible, the best way of survival mechanism isn’t getting rich or being famous or being mighty but to fear the Lord.
For More Articles https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#time #wisdom #fearofgod #might #money #fame #vapor #redeemtime #tomorrow #today #salvation #church #testimony #soulwinning #preaching #Bible #theword #Abiydinsa #scriptures #abiywakumadinsa
ፍጻሜዬን አስታውቀኝ
አቤቱ፥ ፍጻሜዬን አስታውቀኝ፥ የዘመኔ ቍጥሮች ምን ያህል እንደ ሆኑ፥ እኔ ምን ያህል ወደ ኋላ እንደምቀር አውቅ ዘንድ። መዝሙር 39፡4
ይህ የእግዚአብሄር ሰው የልብ ጩኸት ነው፡፡ ይህ በምድር ላይ ያለው ጊዜ አጭር መሆኑን የተረዳ ሰው የልብ ጩኸት ነው፡፡ ይህ በምድር ላይ ሊሰራ ያለው ስራ ሸክም በውስጡ የሚጮህበት ሰው የልብ ጩኸት ነው፡፡
ሰው በምድር ላይ የሚኖረው አንድ ጊዜ ነው፡፡ ሰው በምድር ላይ የሚኖረው በጣም ለአጭር ጊዜ ነው፡፡ ሰው በምድር ላይ ሚሊየን ቀን አይኖርም፡፡ ሰው በምድር ላይ 120 አመት ቢኖር 43830 ቀናት ነው በምድር ላይ የሚኖረው፡፡ ይህ አጭር የምድር ኑሮ በሚገባ ብንጠቀምበትም ባንጠቀምበትም ማለፉ አይቀርም፡፡ በምደ ያለው ህይወታችን በፍሬያማነት ብንጠቀምበትም ባንጠቀምበትም ወደኋላ ማጠንጠን እንችልም፡፡ ሚያዚያ 26 2010 ተመልሶ አይመጣም፡፡
በህይወታችን መድረስ የምንፈልገውን ብዙ ነገሮችን ስናስብ ብዙ ጊዜ በምድር ላይ ያለው ህይወታችን ውስን መሆኑን እንረሳለን፡፡ ስለዚህ ነው ሰው ከመካከላችን ሲጠራ የምንደነግጠው፡፡ ሞት ሁልጊዜ አዲስ የሚሆንብን በተለያዩ ነገሮች ባተሌ ስለሆንንና በምድር ላይ ያለን ኑሮ አጭር መሆኑን ስለምንረሳ ነው፡፡
መዝሙረኛው እንዲህ እያለ ነው፡፡ ዘመኔ አጭር መሆኑን ከረሳሁ ዘመኔን በአግባቡ መጠቀም አልችልም፡፡ ዘመኔ አጭር መሆኑን ከረሳሁ በከንቱ የማባክነው ጊዜ ይበዛል፡፡ ዘመኔ አጭር መሆኑን ካላወቅኩ መልሼ የማላገኘው በስንፍና የማሳልፈው ጊዜ ይበዛል፡፡ ዘመኔ አጭር መሆኑን ካላስብኩ ቅድሚያ በጥሪዬ ላይ ብቻ አላተኩርም፡፡ ዘመኔ አጭር መሆኑን ካላወቅኩ ቅደሚያ በሚሰጠው ላይ ብቻ ለማተኮርና ቅድሚያ ለመስጠት አላስብም አላቅድም፡፡ ዘመኔ አጭር መሆኑን ካላወቅኩ በእቅድና በጥንቃቄ አልኖርም፡፡
መዝሙረኛው እያለ ያለው በምድር ዘላለም እንደማልኖር ካወቅኩ ጊዜዬን በአግባቡ እጠቀምበታለሁ፡፡ በምድር ላይ ያለው ዘመኔ አጭር እንደሆነ ካወቅኩ ቅድሚያ በሚሰጠው ነገር ላይ ብቻ አተኩራለሁ፡፡ በምድር ላይ ያለው ኑሮዬ ውስን መሆኑን ካወቅኩ የማባክነው ጊዜ አይኖርም፡፡ በምድር ላይ ያለው ጊዜዬ አጭር መሆኑን ከተረዳሁ ውስን የሆነው ጊዜዬን በህይወት አላማዬ ላይ ብቻ አጠፋለሁ፡፡ በምድር ላይ ያለው ጊዜዬ አጭር መሆኑን ከተረዳሁ ያለኝን ጊዜ በጥበብ ለመጠቀም እወስናለሁ፡፡
ይህ የሁላችንም የልብ ጩኸት ሊሆን ይገባል፡፡ እግዚአበሄ በዚህ ቀን ነው የምተጠራው ላይለን ይችላል፡፡ ነገር ግን አጭር መሆኑን እንዳንረሳና ካላግባብ እንዳንዝናና ይፈልጋል፡፡
አቤቱ፥ ፍጻሜዬን አስታውቀኝ፥ የዘመኔ ቍጥሮች ምን ያህል እንደ ሆኑ፥ እኔ ምን ያህል ወደ ኋላ እንደምቀር አውቅ ዘንድ። መዝሙር 39፡4
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ያድርጉ!
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ዘመን #ፍፃሜ #አጭር #እድል #ዋጁ #ጥበብ #መተርጎም #ይሳኮር #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ምሪት #ድምፅ #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ
የሰው መጠበቅና የእግዚአብሄር አሰራር
እግዚአብሄር የራሱ አሰራር መንገድ አለው፡፡ እግዚአብሄር በእኛ መጠበቅ ውስጥ የማይገባበት ጊዜ አለ፡፡ እግዚአብሄር ሁሉን ለራሱ ሊያስገዛ የሚችልበት አሰራር አለው፡፡ ከምንም ነገር ውስጥ የተሻለ ነገር ለማውጣት የሚችለበት አሰራር አለው፡፡
እርሱም ሁሉን እንኳ ለራሱ ሊያስገዛ እንደሚችልበት አሠራር፥ ክቡር ሥጋውን እንዲመስል የተዋረደውን ሥጋችንን ይለውጣል። ፊልጵስዩስ 3፡21
ሰው የሚጠብቀው እግዚአብሄር ወዲያው እንዲፈርድ ነው፡፡
ያዕቆብ ሆይ፥ እስራኤልም ሆይ፦ መንገዴ ከእግዚአብሔር ተሰውራለች ፍርዴም ከአምላኬ አልፋለች ለምን ትላለህ? ለምንስ እንዲህ ትናገራለህ? ኢሳያስ 40፡27
እግዚአብሄር የሚፈልገው እርሱ እስኪፈርድ ድረስ ሰው እንዲታገስ ነው፡፡
ሰው የሚጠብቀው በፊቱ ያለው ተራራ እንዲነሳ ነው፡፡
እግዚአብሄር የሚፈልገው አንዳንዴ ሰው ተራራውን እንዲወጣው ነው፡፡ እግዚአበሄር ሃይልን ይሰጣል፡፡
ለደካማ ኃይልን ይሰጣል፥ ጕልበት ለሌለውም ብርታትን ይጨምራል። ኢሳያስ 40፡29
ሰው የሚፈልገው አስቸጋሪ ነገሮች ሁልጊዜ ከፊቱ እንዲነሱ ብቻ ነው፡፡
እግዚአብሄር የሚፈልገው በአስቸጋሪ ነገር ውስጥም ቢሆን ሰው እግዚአብሄርን እንዲያከብር ነው፡፡
ቃሉን ስበክ፥ በጊዜውም አለጊዜውም ጽና፥ 2ኛ ጢሞቴዎስ 4፡2
ሰው የሚፈልገው እንዳይደክም ነው፡፡
እግዚአበሄር የሚፈልገው በራሳችን ብንደክምም እንኳን በክርስቶስ እንድንበረታ ነው፡፡
እርሱም፦ ጸጋዬ ይበቃሃል፥ ኃይሌ በድካም ይፈጸማልና አለኝ። እንግዲህ የክርስቶስ ኃይል ያድርብኝ ዘንድ በብዙ ደስታ በድካሜ ልመካ እወዳለሁ። ስለዚህ ስለ ክርስቶስ በድካም በመንገላታትም በችግርም በስደትም በጭንቀትም ደስ ይለኛል፤ ስደክም ያን ጊዜ ኃይለኛ ነኝና። 2ኛ ቆሮንቶስ 12፡9-10
ሰው የሚፈልገው በነገሮች ደስ እንዲለው ነው፡፡
የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው፥ መፅናናትን ያገኛሉና። ማቴዎስ 5፡4
እግዚአብሄር የሚፈልገው በነገሮችም ብናዝን በእርሱ በጌታ ሁልጊዜ ደስ እንዲለን ነው፡፡
ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ፤ ደግሜ እላለሁ፥ ደስ ይበላችሁ። ፊልጵስዩስ 4፡4
ሰው የሚፈልገው በሁሉ ነገር ተስፋ እንዲኖረው ነው፡፡
እግዚአብሄር የሚፈልገው ተስፋ በሌለን ጊዜ የእግዚአብሄርን ተስፋ ብቻ ይዘን እንድናምን ነው፡፡
ዘርህ እንዲሁ ሊሆን ነው እንደ ተባለ፥ ተስፋ ባልሆነው ጊዜ የብዙ አሕዛብ አባት እንዲሆን ተስፋ ይዞ አመነ። ሮሜ 4፡18
ሰው የሚፈልገው የውጭን ሰላም ነው፡፡
እግዚአብሄር የሚፈልገው በውጭው መረበሽ መካከል ያለውን የውስጥ እውነተኛ ሰላም ነው፡፡
አእምሮንም ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል። ፊልጵስዩስ 4፡7
ሰው የሚፈልገው ሰው በሚታየው ነገር ሁሉ እንዳይጎድል ነው፡፡
እግዚአብሄር የሚፈልገው ብናገኝም ባናገኝም በክርስቶስ ሁሉን እንድንችል ነው፡፡
መዋረድንም አውቃለሁ መብዛትንም አውቃለሁ፤ በእያንዳንዱ ነገር በነገርም ሁሉ መጥገብንና መራብንም መብዛትንና መጉደልን ተምሬአለሁ። ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ። ፊልጵስዩስ 4፡12-13
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #መኖሪያህእግዚአብሄር #እውቀት #ጥበብ #ሃይል #እንፍዋለት #አልፋ #ኦሜጋ #መጀመሪያ #መጨረሻ #ክርስትያን #አማርኛ #መደገፍ #ማስተዋል #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #አዲስፍጥረት #ፅድቅ #ማመን #አይመረመርም #ስልጣን
ማስተዋሉም አይመረመርም
ያዕቆብ ሆይ፥ እስራኤልም ሆይ፦ መንገዴ ከእግዚአብሔር ተሰውራለች ፍርዴም ከአምላኬ አልፋለች ለምን ትላለህ? ለምንስ እንዲህ ትናገራለህ? አላወቅህምን? አልሰማህምን? እግዚአብሔር የዘላለም አምላክ፥ የምድርም ዳርቻ ፈጣሪ ነው፤ አይደክምም፥ አይታክትም፥ ማስተዋሉም አይመረመርም። ኢሳይያስ 40፡17-18
የእስራኤል ህዝብ እግዚአብሄር እኛን አያየንም መንገዳችንን አያውቅም፡፡ የእስራኤል ህዝብ እንደተረሱ እንደማይታዩ ተሰምቶዋቸው የነበረበት ጊዜ ነበር፡፡
ስሜታችንን መስማት ባይኖርብንም አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሄር ሩቅ እንደሆነ እንደማይሰማ እንደማያይ እንደማይፈርድ የሚሰማን ጊዜ አለ፡፡ ትክክለኛውን ነገር እንዳረግን እየተሰማን ነገሮች እንደምንፈልጋቸው ሳይሄዱ ሲቀሩ እውነት እግዚአብሄር ያያል? ብለን እንጠይቃለን፡፡ ሁሉንም ነገር ትክክል ካደረግን በኋላ ይሰምራል ያልነው ነገር እንዳሰብነው ሳይሰምር ሲቀሩ የሚሰማንን ስሜት ነበር የእስራኤል ህዝብን ይሰማው የነበረው፡፡
የእስራኤል ህዝብ እግዚአብሄር ፍርድን አይፈርድም ብለው ያስቡ ነበር፡፡ በፅድቅ ኖሬ እግዚአብሄር ይፈርድልኛል ብሎ በሚያስበው ሁኔታ እግዚአብሄር ሳይፈርድ ሲቀር እስራኤል በእግዚአብሄር ላይ ይናገር ነበር፡፡ በትክክል ከኖረ በኋላ እግዚአብሄር ነገሮችን ያስተካክላል ብሎ ባሰበው ሁኔታ ነገሮች ስላልተስተካከሉ እስራኤል የተሰማው ስሜት የተስፋ መቁረጥ ስሜት ነበር፡፡
አምላካዊ መልሱ ግን እግዚአብሄር የዘላለም አምላክ ነው የሚል ነው፡፡ እግዚአብሄር መሪነትን እየተለማመደ ያለ ጀማሪ መሪ አይደለም፡፡ እግዚአብሄር እየሞከረ እየተሳሳተ የሚለምድ ተለማማጅ መሪ አይደለም፡፡ እግዚአብሄር የማያወቀውን እያወቀ ልምድን በማካበት የተሻለ መሪ ለመሆን የሚጥር መሪ አይደለም፡፡ እግዚአብሄር የዘላለም አምላክ ነው፡፡
ብቻውን አምላክ ለሚሆን ለማይጠፋው ለማይታየውም ለዘመናት ንጉሥ ምስጋናና ክብር እስከ ዘላለም ድረስ ይሁን፤ አሜን። 1ኛ ጢሞቴዎስ 1፡17
እግዚአብሄር ጠላቶቹን አሸንፎ የነገሰ ንጉስ አይደለም፡፡ እግዚአብሄር የዘመናት ንጉስ ነው፡፡
እግዚአብሔር ግን እውነተኛ አምላክ ነው፤ እርሱም ሕያው አምላክና የዘላለም ንጉሥ ነው፤ ኤርሚያስ 10፡10
እግዚአብሄር የምድር ዳርቻ ፈጣሪ ነው፡፡ እግዚአብሄር በምድር ውስጥ ያለውን ሁሉ ነገር የፈጠረና የሚያስተዳደር ነው፡፡ እግዚአብሄር የባህር ዳርቻን የወሰነ ነው፡፡
ለባሕርም ዳርቻን በወሰነ ጊዜ ውኃ ከትእዛዙ እንዳያልፍ፥ የምድርን መሠረት በመሠረተ ጊዜ፥ ምሳሌ 8፡29
የእግዚአብሄር ማስተዋሉ አይመረመርም፡፡ እግዚአብሄርንም ሙሉ ለሙሉ ለመረዳት እኛ ራሳችን እግዚአብሄር መሆን አለብን፡፡ በፍጥረት አቅማችን እግዚአብሄን ሙሉ ለሙሉ አናውቀውም፡፡
እነሆ፥ እግዚአብሔር ታላቅ ነው፥ እኛም አናውቀውም። የዘመኑም ቍጥር አይመረመርም። ኢዮብ 36፡26
ሰው ማድረግ የሚችለው አንድ የተሻለ ነገር በእግዚአብሄር መልካምነትና ሃያልነት ላይ መደገፍ ብቻ ነው፡፡ ሰው እግዚአብሄር በእርሱ ላይ ባለው የፍቅር አላማ ላይ ከመደገፍ በላይ ምንም ተስፋ የለውም፡፡
ያዕቆብ ሆይ፥ እስራኤልም ሆይ፦ መንገዴ ከእግዚአብሔር ተሰውራለች ፍርዴም ከአምላኬ አልፋለች ለምን ትላለህ? ለምንስ እንዲህ ትናገራለህ? አላወቅህምን? አልሰማህምን? እግዚአብሔር የዘላለም አምላክ፥ የምድርም ዳርቻ ፈጣሪ ነው፤ አይደክምም፥ አይታክትም፥ ማስተዋሉም አይመረመርም። ኢሳይያስ 40፡17-18
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #መኖሪያህእግዚአብሄር #እውቀት #ጥበብ #ሃይል #እንፍዋለት #አልፋ #ኦሜጋ #መጀመሪያ #መጨረሻ #ክርስትያን #አማርኛ #መደገፍ #ማስተዋል #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #አዲስፍጥረት #ፅድቅ #ማመን #አይመረመርም #ስልጣን
ኤፕሪል ዘ ፉል
በየአመቱ ኤፕሪል 1 ቀን የማሞኛ ቀን ተብሎ በብዙ ሰዎች ዘንድ ሰውን ዋሽቶ ማታለል እንደመዝናኛ ይቆጠራል፡፡ አንዳንድ ሰው ሰውብ ማስደንገጥ ደስ የሚለው ሰው አለ፡፡ እኔ በበኩሌ ሰውን ማስደንገጥ በፍፁም አልወድም፡፡
ትንታግንና ፍላጻን ሞትንም እንደሚወረውር እንደ ዕብድ ሰው፥ ባልንጀራውን የሚያታልል፦ በጨዋታ አደረግሁት የሚል ሰውም እንዲሁ ነው። ምሳሌ 26፡18-19
ሰው ሰውን ሊያታልለው ይችላል፡፡ አንዳንድ ሰው ግን ራሱን ያታልላል፡፡ በጣም በአስፈላጊ እና ወሳኝ ነገር ላይ ራሱን የሚያታልል ሰው እንዳለ መፅሃፍ ቅዱስ ያስተምረናል፡፡
ሰነፍ በልቡ፦ አምላክ የለም ይላል። በሥራቸው ረከሱ፥ ጐስቈሉ፤ በጎ ነገርን የሚሠራ የለም። መዝሙር 14፡1
The fool says in his heart, “There is no God.” They are corrupt, their deeds are vile; there is no one who does. Psalm 14:1
የሚገርመው ነገር ሰነፍ በልቡ ነው እግዚአብሄር የለም የሚለው፡፡ እግዚአብሄር የለም ማለቱ የሚታወቀው በድርጊቱ ብቻ ነው፡፡ የሚኖረው ኑሮ ሁሉ እግዚአብሄር እንደሌለ ነው የሚያሳየው፡፡ እግዚአብሄር የለም ብሎ ያስባል፡፡ እግዚአብሄር እንደሌለ እንደማይፈርድ አድርጎ ያስባል፡፡ እግዚአብሄር እንደሌለ እንደማይሰራ አድርጎ ይናገራል፡፡ እግዚአብሄር እንደሌለ የፈለገውን ማድረግ እንደሚችል አድርጎ ይመላለሳል፡፡
ሰነፍ በልቡ፦ አምላክ የለም ይላል። ረከሱ በበደላቸውም ጐሰቈሉ፤ በጎ ነገርን የሚያደርጋት የለም። መዝሙር 53፡1
እግዚአብሄር የለም የሚል ሰው ተጠያቂነትን አይፈልግም፡፡ እግዚአብሄር የለም የሚል ሰው ራሱን መግዛት አይፈልግም፡፡ እግዚአብሄር የለም የሚል ሰው ለማንም ተጠሪ መሆን አይፈልግም፡፡ እግዚአብሄር የለም የሚል ሰው እንደልቡ መኖር ነው የሚፈልገው፡፡
ሰው እግዚአብሄር አለ ካለ እግዚአብሄርን በየእለቱ መፈለግ አለበት፡፡ ሰው እግዚአብሄር አለ ካለ የእግዚአብሄርን ፈቃድ መፈለግና መከተል አለበት፡፡ ሰው እግዚአብሄር አለ ብሎ ካመነ እግዚአብሄርን በነገር ሁሉ መፍራት አለበት፡፡ ሰው እግዚአብሄር አለ ካለ ለእግዚአብሄር ተጠያቂነት አለበት፡፡
ሰነፍ ወይም ሞኝ ለስንፍናው ማሳበቢያ የሚያገኘው እግዚአብሄር የለም በማለት ነው፡፡ እግዚአብሄር የለም በማለቱ እግዚአብሄርን ከመፈለግ ፣ ፈቃዱን ከማድረግና ለእግዚአብሄር ካለ የህይወት ሃላፊነቶች ሁሉ የዳነ ይመስለዋል፡፡ በዚህም ራሱን ያታልላል፡፡
ሰው ጥበበኝነቱና ትጋቱ የሚታወቀው ለእግዚአብሄር መኖር እውቅና በመስጠቱ ብቻ ነው፡፡
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ሰነፎች ግን ጥበብንና ተግሣጽን ይንቃሉ። ምሳሌ 1፡7
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ጥበብ #ቤተክርስትያን #ሞኝ #ሰነፍ #በልቡ #እግዚአብሔር #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ማስተዋል #እምነት #ፈተና #ፀሎት #ጌታ #የእግዚአብሄርቃል #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
የባሰውን ፍርድ እንድንቀበል ታውቃላችሁ
ወንድሞቼ ሆይ፥ ከእናንተ ብዙዎቹ አስተማሪዎች አይሁኑ፥ የባሰውን ፍርድ እንድንቀበል ታውቃላችሁና። ያዕቆብ 3፣1
አስተማሪዎች ቢበዙ ብዙ ሰዎች ይታነፃሉ ብዙ ሰዎች ይለወጣሉ፡፡ አስተማሪነት ግን ታላቅ ተፅእኖ እንደሚያመጣ ሁሉ ታላቅም ሃላፊነት አለበት፡፡
አስተማሪ የሰዎችን አእምሮ በመለወጥ ህይወታቸውንም የመለወጥ ታላቅ ስልጣን ያለው አገልግሎት ነው፡፡
እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ፥ እርሱም ለአእምሮ የሚመች አገልግሎታችሁ ነው። የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ። ሮሜ 12፡2
ሰዎች የስህተት አስተምህሮ ሰምተው ሃይማኖትን እስከመካድ ይደርሳሉ፡፡ ሰዎች እውነተኛ አስተማሪን ሰምተው ከስህተት ይመለሳሉ፡፡
መንፈስ ግን በግልጥ፦ በኋለኞች ዘመናት አንዳንዶች የሚያስቱ መናፍስትንና በውሸተኞች ግብዝነት የተሰጠውን የአጋንንትን ትምህርት እያደመጡ፥ ሃይማኖትን ይክዳሉ ይላል፤ በገዛ ሕሊናቸው እንደሚቃጠሉ ደንዝዘው፥ 1ኛ ጢሞቴዎስ 4፡1-2
በተፈጥሮ ሰው ለትክክለኛ እድገትና ብስለት ምግብ ብቻ ሳይሆን የተመጣጠነ ምግብ ያስፈልገዋል፡፡ ሰው አንድ አይነት ምግብ ብቻ ከበላና ጉልበት የሚሰጠው ፣ ከበሽታ የሚከላከልለትና የሚገነባው የተሟላ ምግብ ካልበላ ጤነኛ አይሆንም፡፡
እንዲሁም ሰዎች ሚዛኑን ያልጠበቀ በአንድ ወገን ብቻ የተለጠጠ ትምህርትን አስተምረው የሚሰሟቸውን ለመንፈሳዊ በሽተኝነት ያጋለጣሉ፡፡
ስለዚህ አስተማሪነት እውቀት ብቻ ሳይሆን እውቀትን እንዴት ማስተላለፍ እንደሚያስፈልግ ጥበብን ይጠይቃል፡፡ አስተማሪነት እውቀት ማግኘት ብቻ ሳይሆን እውቀትን ሚዛናዊነቱን ጠብቆ ማስተላለፍን ይጠይቃል፡፡
ዛሬ የምናስተምረው ትምህርት ነገ ለምናስተምረው ትምህርት እንቅፋት የሚሆን ከሆነ ሚዛኑን አልጠበቀም፡፡ በባህሪው ስጋዊ ባህሪያችን ማጋነን ይወዳል፡፡ ስናስተምር ትምህርቱን ለማጋነን እንፈተናለን፡፡ ትምህርትን ማጋነን ግን እንዳውም ሃይሉን ያሳጣዋል እንጂ አያጠናክረውም፡፡
ባስተላለፋችሁትም ወግ የእግዚአብሔርን ቃል ትሽራላችሁ፤ እንደዚሁም ይህን የሚመስል ብዙ ነገር ታደርጋላችሁ። ማርቆስ 7፡13
ስናስተምር በጣም ትምህርቱን ከሚገባው በላይ ከመለጠጣችን የተነሳ ከፅንፉ ለመመለስ ድፍረቱ ከሌለን ሰውን እያሳሳትን ነው፡፡ ዛሬ የምናስተምረው ትምህርት ነገ ለምናስተምረው ትምህርት እንቅፋት ከሆነ ሚዛኑን ያልጠበቀ ትምህርት እያስተማርን ሰውን ግራ እያጋባን እንዲሁም ከማበርታት ይልቅ እያደከምነው ነው፡፡ ዛሬ የምናስተምረው ትምህርት ነገ ማስተማር ካለብን ትምህርት ጋር የሚጋጭ ከሆነ ተጋኗል፡፡
አስተማሪዎች ስንሆን አንዳንዱን ብቻ ሳይሆን መሉውን የእግዚአብሄር ምክር ማስተማር አለብን፡፡
የእግዚአብሔርን ምክር ሁሉ ነግሬአችኋለሁና፥ ምንም አላስቀረሁባችሁም። ሐዋርያት 20፡27
ሙሉው የእግዚአብሄር ምክር ነው የሚማሩትን ሰዎች ወደ ሙላት የሚያመጣው፡፡
ከተሳሳትን ደግሞ ይቅርታ ባለፈው ያስተማርኩት ትምህርት ስህተት ነበር ብለን ፈጥነን ማስተካከል ይጠብቅብናል፡፡
እውቀት ስላለን ብቻ አናስተምርም፡፡ በእግዚአብሄር ፊት እንፀልያለን፡፡ እግዚአብሄር በልባችን የሚያፈሰውን መልክት ይዘን እናጠናለን እንዘጋጃለን፡፡ መልክቱን ጊዜ ወስደን እናወጣለን እናወርዳለን፡፡ እንዴት እንደምናስተላልፈው ከእግዚአብሄር ጥበብን እንጠይቃለን፡፡ የባሰውን ፍርድ እንድንቀበል አውቀን በትህትና በፍርሃት ሁሉ እናስተምራለን፡፡
ወንድሞቼ ሆይ፥ ከእናንተ ብዙዎቹ አስተማሪዎች አይሁኑ፥ የባሰውን ፍርድ እንድንቀበል ታውቃላችሁና። ያዕቆብ 3፣1
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ማስተማር #ቃል #ማሰላሰል #የእግዚአብሄርቃል #ሚዛን #ምክር #አስተማሪ #መምህር #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #አእምሮ #ፍርድ #ፅናት #ትግስት #መሪ
በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ
ከሰው ይልቅ የእግዚአብሔር ሞኝነት ይጠበባልና
ከሰው ይልቅ የእግዚአብሔር ሞኝነት ይጠበባልና፥ የእግዚአብሔርም ድካም ከሰው ይልቅ ይበረታልና። 1ኛ ቆሮንቶስ 1፡25
የሰው ጥበብ ሲጨርስ የእግዚአብሄር ጥበብ ይጀምራል፡፡ የእግዚአብሄር ሞኝነት የሰውን እጅግ ታላቅ ጥበብ ይበልጠዋል፡፡ የእግዚአብሄር ድካም ከሰውን እጅግ ታላቅ ሃይል ይበረታል፡፡
ከሰው እጅግ ታላቅ ጥበብ ይልቅ የእግዚአብሄር ሞኝነት ይሻላል፡፡ በሰው እጅግ ታላቅ ጥበብ ከመደገፍ ይልቅ በእግዚአብሄር ሞኝነት መደገፍ ይሻላል፡፡
የእግዚአብሄር ማስተዋል ጥልቅ ነው፡፡
አላወቅህምን? አልሰማህምን? እግዚአብሔር የዘላለም አምላክ፥ የምድርም ዳርቻ ፈጣሪ ነው፤ አይደክምም፥ አይታክትም፥ ማስተዋሉም አይመረመርም። ኢሳያስ 40፡28
ስለዚህ ነው ማንም አንዳች የሚያውቅ ቢመስለው ሊያውቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም የሚለው፡፡
ማንም አንዳች የሚያውቅ ቢመስለው ሊያውቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም፤ 1ኛ ቆሮንቶስ 8፡1
በራስ ማስተዋል እንደመደገፍ አደገኛ ነገር የለም፡፡ የእኛ ማስተዋል ልንደገፍበት የሚበቃ አይደለም፡፡ ሰው በሸንበቆ ላየ ዘና ብሎ እንደማይደገፍ ሁሉ የእኛ ማስተዋል ለመደገፍ የማይበቃ ደካማ ነው፡፡ ስለዚህ ነው መፅሃፍ ቅዱስ በራስህ ማስተዋል አትደገፍ የሚለው፡፡ የትኛውም የእኛ ማስተዋል ልንደገፍበት በቂ አይደለም፡፡ የእኛ እጅግ ታላቁ ማስተዋል የእግዚአብሄርን ጥበብ አይደለም ሞኝነቱን አይደርስበትም፡፡
በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤ በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ፥ እርሱም ጎዳናህን ያቀናልሃል። ምሳሌ 3፡5-6
ስለዚህ ነው መፅሃፍ ቅዱስ በመንገድህ ሁሉ አርሱን እወቅ የሚለው፡፡ በመንገድህ ሁሉ ለእርሱ አዋቂነት እውቅና ስጥ፡፡ በመንገድህ ሁሉ እኔ ለራሴ ከማውቀው በላይ እርሱ ለእኔ ያውቃል በል፡፡ በመንገድህ ሁሉ እኔ የማላውቀው ነገር አለ እርሱ ሁሉን ያውቃል በል፡፡ በመንገድህ ሁሉ እኔ ልሳሳት እችላሁ አርሱ ግን አይሳሳትም በል፡፡
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#እውቀት #ጥበብ #ማስተዋል #ቃል #መልካም #መታመን #መደገፍ #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
የአባካኙ ልጅ ታሪክ
እንዲህም አለ፦ አንድ ሰው ሁለት ልጆች ነበሩት። ከእነርሱም ታናሹ አባቱን፦ አባቴ ሆይ፥ ከገንዘብህ የሚደርሰኝን ክፍል ስጠኝ አለው። ገንዘቡንም አካፈላቸው። ከጥቂት ቀንም በኋላ ታናሹ ልጅ ገንዘቡን ሁሉ ሰብስቦ ወደ ሩቅ አገር ሄደ፥ ከዚያም እያባከነ ገንዘቡን በተነ። ሁሉንም ከከሰረ በኋላ በዚያች አገር ጽኑ ራብ ሆነ፥ እርሱም ይጨነቅ ጀመር። ሄዶም ከዚያች አገር ሰዎች ከአንዱ ጋር ተዳበለ፥ እርሱም እሪያ ሊያሰማራ ወደ ሜዳ ሰደደው። እሪያዎችም ከሚበሉት አሰር ሊጠግብ ይመኝ ነበር፥ የሚሰጠውም አልነበረም። ወደ ልቡም ተመልሶ እንዲህ አለ፦ እንጀራ የሚተርፋቸው የአባቴ ሞያተኞች ስንት ናቸው? እኔ ግን ከዚህ በራብ እጠፋለሁ። ተነሥቼም ወደ አባቴ እሄዳለሁና፦ አባቴ ሆይ፥ በሰማይና በፊትህ በደልሁ፥ ወደ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም፤ ከሞያተኞችህ እንደ አንዱ አድርገኝ እለዋለሁ። ተነሥቶም ወደ አባቱ መጣ። እርሱም ገና ሩቅ ሳለ አባቱ አየውና አዘነለት፥ ሮጦም አንገቱን አቀፈውና ሳመው። ልጁም፦ አባቴ ሆይ፥ በሰማይና በፊትህ በደልሁ፥ ወደ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም አለው። ሉቃስ 15፡11-21
አባካኙ ልጅ ከአባቱ ጥላ መውጣትን አልፈራም
አባካኙ ልጅ አባቱ ያደርግለት የነበራቸውን ነገሮች እንደአስፈላጊ ነገር በፍፁም አላያቸውም፡፡ አባካኙ ልጅ የአባቱን ጥበቃ ዋጋ አልሰጠውም ነበር፡፡ አባካኙ ልጅ የአባቱን እቅርቦት ከምንም አልቆጠረውም ነበር፡፡ አባቱ በቀላሉ የሚያቀርበለት ነገር ሰዎች በህይወት ዘመናቸው ቢሰሩለትና ቢለፉለትን እንኳን እንደማያገኙት ሲረዳ ብቻ ነው የአባቱን አቅርቦት አውቅና የሰጠው፡፡ አባቱ ምን ያህል ይንከባከበው እንደነበር ያወቀው የቤታቸው ባሮች በልተው የሚተርፋቸውን ምግብ አጥቶ ሲያየው ብቻ ነው፡፡
አባካኙ ልጅ የቤተሰብን ዋጋ መረዳት አልቻለም
አባካኙ ልጅ የሚያውቁት የሚወዱት ሰዎች መካካል መኖሩን እንደጥቅም አላየውም፡፡ አባካኙ ልጅ ዋጋውን የሚያውቁ የሚያከብሩት የእኛ የሚሉት የሚጠነቀቁለት የቤተሰቦቹን እርዳታ ከምንም አልቆጠረውም፡፡ የቤተሰብን ጥቅም ያወቀው ምንም የማያውቁት ሰዎች መካከል ሲኖርና የማንም ልጅ እንደሆነ የማያውቁትና ዝቅ አድርገው የሚመለከቱት መካከል ሲገባ ነው፡፡
አባካኙ ልጅ ከአባቱ ምሪት መውጣትን አልፈራም
አባካኙ ልጅ በአባቱ መሪነት ሲያድግና ሲኖር ነበር የቆየው፡፡ በአባቱን ምሪት ሲጠቀም ቆይቶዋል፡፡ የአባት ምሪት ምን ያህል ጠቃሚ እንደሆነ ያወቀው የአባቱን ምክር ያጣው ጊዜ ብቻ ነው፡፡ ከአባቱ ሲርቅ ከአባቱ ምክር ራቀ፡፡ ገንዘቡን እንዴት እንደሚጠቀም የሚመራው አባቱ ነበር፡፡ ቅድሚያ የሚሰጠውና ቅድሚያ የማይሰጠውንም ነገር ለይቶ የሚነግረው አባቱ ነበር፡፡ ከአባቱ ሲለይ ግን ገንዘቡን ማጥፋት በሌለበት ነገር ላይ አጠፋ፡፡ ገንዘቡ ሲያልቅ ነበር እንዳባከነው ያወቀው፡፡
አባካኙ ልጅ የሚያውቅ መስሎት ነበር
አባካኙ ልጅ ለራሱ የተሳሳተ ግምት ነበረው፡፡ አባካኙ ልጅ የሚያውቅ ይመስለው ነበር፡፡ አባካኙ ልጅ እንደማያውቅ ያወቀው ከወደቀ በኋላ ነው፡፡ ማወቅ የሚገባውን ያህል እንዳላወቀ የተረዳው ህይወቱ ከባከነ በኋላ ነበር፡፡ አባካኙ ልጅ ከሆነው በላይ ትልቅ ሰው የሆነ መሰለው፡፡ ወደ ልቡ ሲመለስ ብቻ ነው ማወቅ የሚገባውን ያህል እነዳላወቀ ያወቀው በዚያም ምክኒያት ሁሉ ነገር እንደተዛባ ያወቀው፡፡
አባካኙ ልጅ ነፃነት ያለውን ሃላፊነት አልተረዳም
አባካኙ ልጅ ነፃ መሆን ፈለገ፡፡ አባካኙ ልጅ ለአባቱን ተጠሪ መሆንን አልፈለገውም፡፡ አባካኙ ልጅ የአባቱን አገዛዝ ከራሱ ላይ መጣል ፈለገ፡፡ ነገር ግን አባካኙ ልጅ ያልተረዳው ነገር ነፃነት የራሱ ሃላፊነት እንዳለበት ነው፡፡ ከሃላፊነት ውጭ የሆነ ነፃነት የለም፡፡ ለአባቱ መሪነት ተጠሪ ካልሆነ ለህሊናው ተጠሪ መሆን ነበረበት፡፡ ሃላፊነት የሌለበት ፍፁም ነፃነት የሚባለ ነገር የለም፡፡ ሁላችንም የአንድ ነገር አገልጋዮች ወይም ባሪያዎች ነን፡፡ ጥያቄው ባሪያ መሆንና አለመሆን ሳይሆን የምን ባሪያዎች መሆናችን ነው፡፡
ለመታዘዝ ባሪያዎች እንድትሆኑ ራሳችሁን ለምታቀርቡለት፥ ለእርሱ ለምትታዘዙለት ባሪያዎች እንደ ሆናችሁ አታውቁምን? ወይም ለሞት የኃጢአት ባሪያዎች ወይም ለጽድቅ የመታዘዝ ባሪያዎች ናችሁ። ነገር ግን አስቀድማችሁ የኃጢአት ባሪያዎች ከሆናችሁ፥ ለተሰጣችሁለት ለትምህርት ዓይነት ከልባችሁ ስለ ታዘዛችሁ፥ ከኃጢአትም አርነት ወጥታችሁ ለጽድቅ ስለ ተገዛችሁ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን። ሮሜ 6፡16-18
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ማክበር #መደሰት #አባት #ቤተሰብ #ጥላ #በረከት #ስኬት #እረኛእግዚአብሄር #ስምረት #እውቀት #ሁሉየእናንተነውና #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #የተትረፈረፈህይወት #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #መርካት #ደስታ #ማስተዳደር #እረፍት
ክፉውን አትቃወሙ
እኔ ግን እላችኋለሁ፥ ክፉውን አትቃወሙ፤ ዳሩ ግን ቀኝ ጉንጭህን በጥፊ ለሚመታህ ሁሉ ሁለተኛውን ደግሞ አዙርለት፤ ማቴዎስ 5፡39
በህይወቱ የሚያየውን ክፉ ሁሉ በክፉ ለመመለስ የሚያስብ ሰው የክርስትናን ህይወት በሚገባ አልተረተዳውም፡፡
በአለም የሚኖሩ ሰዎች ውድድራቸው በክፋት ነው፡፡ ክፉ ያደረገ ሰው ይከበራል፡፡ እጅግ ክፉ ያደረገ ሰው ደግሞ ይበልጥ ይከበራል፡፡ በአለም ያለው ውድድር የእኔነት ውድድር ነው፡፡ ሰው በአለም እኔነቱን ለማሳየት ክፉን ሲያደርግ ክፋትን ሲጨምር በክፉ ሲበልጥ ይታያል፡፡
በአለም ያለ ሰው አሸናፊነቱ ክፉን በክፉ በማሸነፍ ነው፡፡ ክፉን በክፉ የሚያሸነፈ ሰው ይከበራል፡፡ በአለም ክፉን በክፉ አለማሸነፍ ደካማነት ነው፡፡ በአለም ክፉን በእጅግ ክፉ ማሸነፍ ደግሞ ጀግንነት ነው፡፡ በአለም ሰዎች በክፋታቸው ይመካሉ፡፡
በእግዚአብሄር ቤት ግን የሚያስከብረው ክፉን የመቋቋም ችሎታ ነው፡፡ በክርስትና የሚያስከብረው ክፉን የምናሸነፍበትን ፀጋ ማሳየት መግለፅ ነው፡፡ በክርስትና አሸናፊነት ክፉ ያደረጉበትን ሰው በክፋቱ ሳይሸነፉ መልካም ሲያደርጉለት ነው፡፡
ክፉውን በመልካም አሸንፍ እንጂ በክፉ አትሸነፍ። ሮሜ 12፡21
በአለም በክፉ የሚሸነፍ ሰው የተለመደ ነው፡፡ ማንም መንገደኛ በክፉ ይሸነፋል፡፡ በክርስትና በክፉ የሚሸነፍ ሰው ደካማ ነው፡፡
ጠላትህ ግን ቢራብ አብላው፤ ቢጠማ አጠጣው፤ ይህን በማድረግህ በራሱ ላይ የእሳት ፍም ትከምራለህና። ሮሜ 12፡20
በእግዚአብሄር ቤት ከአለም ሰዎች የተለየ በእኛ የሚሰራ ፀጋ እንዳለን የምናሳየው ክፉን በመልካም በመለመለስ ነው፡፡ ከሌሎች የተለየ የእግዚአብሄር ሃይል በውስጣችን እንደሚሰራ የምናሳየው በክፉ ባለመሸነፍ ነው፡፡
ከአለምና ከምድራዊ የተለየ የተሻለ መንገድ የምናሳየው በክፉ ባለመሸነፍ ነው፡፡ የክፉን ህሊናውን የምንነካው ለክፋቱ ክፋት ባለመመለስ ነው፡፡ ክፉን የምናነቃው ለክፋቱ ክፋት ሲጠብቅ መልካምን በመመለስ ነው፡፡ ክፉ የሚደነግጠውና ሌላ አሰራርና ሌላ መንግስት እንዳለ የሚያስበው ክፉን በመልካም የሚመልስ ሰው ሲገጥመው ነው፡፡
በክፉ የማይሸነፍ በመልካም የሚያሸነፍ የተለየ የሚያስችል ሃይል እና ፀጋ እንዳለን የምንመሰክረው በክፉ ባለመሸነፍ በመልካም በማሸነፍ ነው፡፡ ክፉ ይህንም የተለየ ፀጋ እንዲቀናበትና ለራሱ እንዲፈልገው የሚያደርገው ክፉን በመልካም የሚሸንፍ ልዩ ሃይል እንዳለን ሲያይ ነው፡፡
ሰው እናንተ የተለያችሁ ሰዎች ናችሁ የእናንተ ጌታ የእኔ ጌታ እንዲሆን እንፈልጋለሁ የሚለው ክፉን በመልካም የምናሸንፍበትን ከዚህ አለም ያልሆነ መልኮታዊ ሃይል ሲያይ ነው፡፡
እንዲከስህም እጀ ጠባብህንም እንዲወስድ ለሚወድ መጎናጸፊያህን ደግሞ ተውለት፤ ማንም ሰው አንድ ምዕራፍ ትሄድ ዘንድ ቢያስገድድህ ሁለተኛውን ከእርሱ ጋር ሂድ። ማቴዎስ 5፡40-41
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #መሪ #ፀጋ #የሚያስችልሃይል #ብቃት #የእግዚአብሄርችሎታ #የእግዚአብሄርሃይል #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ትጋት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ፅድቅ #እግዚአብሄርንመምሰል #ራስንመግዛት #ልብ #ምስክርነት
የህይወት ጥያቄ አንድ መልስ የለውም
የህይወት ጥያቄ አንድ መልስ የለውም፡፡ የህይወት ጥያቄ ብዙ ነው፡፡ የህይወት ጥያቄ ውስብስብ ነው፡፡ ነገር ግን የህይወት ጥያቄ ሁሉ መልስ አለው፡፡ ውስብስብ ለሆነ የህይወት ጥያቄ ቀላል መልስ መመለስ ሞኝነት ነው፡፡ ለዘርፈ ብዙ የህይወት ጥያቄ አንድ መልስ ለመመለስ መሞከር ስህተት ነው፡፡
የህይወት ጥያቄ አንድ መልስ የለውም፡፡ የህይወት ጥያቄ አንድ ነጠላ ስላይደለ መልሱም አንድ ነጠላ ሊሆን አይችልም፡፡
የህይወት ጥያቄን አንዴ መልሰን የምንገላገለው አይደለም፡፡ የህይወት ጥያቄ ለረጅም ጊዜ እየፈታን እየፈታን የምንሄደው ነው፡፡ በእግዚአብሄር ላይ ከመደገፍ ይልቅ የህይወት ጥያቄን በራሳችን ለመፍታትና ለመገላገል መሞከር እግዚአብሄርን ደስ አያሰኘውም፡፡ እግዚአብሄር ስለ ጥያቄያችን በእያንዳንዱ ቀን ሁሌ እንድንደገፍበት ይፈልጋል፡፡
ነገ ለራሱ ይጨነቃልና ለነገ አትጨነቁ፤ ለቀኑ ክፋቱ ይበቃዋል። ማቴዎስ 6፡34
እንዲህ አደርጋለሁ፤ ጐተራዬን አፍርሼ ሌላ የሚበልጥ እሠራለሁ፥ በዚያም ፍሬዬንና በረከቴን ሁሉ አከማቻለሁ፤ ነፍሴንም፦ አንቺ ነፍሴ፥ ለብዙ ዘመን የሚቀር ብዙ በረከት አለሽ፤ ዕረፊ፥ ብዪ፥ ጠጪ፥ ደስ ይበልሽ እላታለሁ አለ። ሉቃስ 12፡18-19
የሰው ባህሪ ለህይወት ጥያቄ አንድ መልስ አግኝቶ ቢያርፍ ደስ ይለዋል፡፡ የህይወት ጥያቄ ግን እንደዚያ አይመለስም፡፡ ሰው ለውስብስቡ የህይወት ጥያቄ ቀላል መልስ መልሶ እፎት ቢል ደስተኛ ነው፡፡ ነገር ግን የህይወት ጥያቄ እንደዚያ አይመለስም፡፡ ወይም ደግሞ ሰው አንዴ የህይወትን ጥያቄ መልሶ ሁለተኛ ባይጠየቅ ደስታው ነው፡፡ የህይወት ጥያቄን ለመመለስ ረጅም ቀጣይነት ያለው ስራን ይጠይቃል፡፡
ከአዛሄልም ሰይፍ ያመለጠውን ሁሉ። ኢዩ ይገድለዋል፤ ከኢዩም ሰይፍ ያመለጠውን ሁሉ ኤልሳዕ ይገድለዋል። 1ኛ ነገሥት 19፡17
ለተሳካ ህይወት ጥበብ ወሳኝ ስለዚህ ነው፡፡ ጥበብ ካለን ለያንዳንዱ የህይወት ጥያቄ መልስ መስጠት እንችላለን፡፡
የህይወት ጥያቄ ብዙ ስለሆነ ብዙ ጥበብ ያስፈልገናል፡፡ ብዙ ጥበብ ባገኘን መጠን ጥያቄዎችን የመፍታት አቅማችን ይጨምራል፡፡ ጥበብን በልግስና የተቀበለ ሰው ጥያቄዎችን ለመመለስ የተሻለ አቅም ይኖረዋል፡፡
ከእናንተ ግን ማንም ጥበብ ቢጎድለው፥ ሳይነቅፍ በልግስና ለሁሉ የሚሰጠውን እግዚአብሔርን ይለምን፥ ለእርሱም ይሰጠዋል። ያዕቆብ 1፡5
የህይወት ጥያቄ ዘርፈ ብዙ ስለሆነ ጥበብም ዘርፈ ብዙ ነው፡፡ ለዘርፈ ብዙ ተግዳሮት ልዩ ልዩ ጥበብ ይጠይቃል፡፡
ብዙ ልዩ ልዩ የእግዚአብሔር ጥበብ አሁን በቤተ ክርስቲያን በኩል በሰማያዊ ስፍራ ውስጥ ላሉት አለቆችና ሥልጣናት ትታወቅ ዘንድ፤ ኤፌሶን 3፡10
ሰይጣን የሚመጣው በተለያዩና በብዙ አቅጣጫዎች ነው፡፡ ሰይጣን በግል ህይወት ፣ በስራ ፣ በቤተሰብ ፣ በትዳር ፣ በቤተክርስትያን ፣ በጓደኛ ፣ በዘመድ በመሳሰሉት ሁሉ ይምጣል፡፡ አንዱን የፈታችሁበት መንገድ ለሌላው አይሰራም፡፡ ለአንዱ የመለሳችሁት መልስ ለሌላው ትክክለኛ መልስ አይሆንም፡፡
በመፀለይ የሚመለስ ጥያቄ አለ ፣ ቃሉን በመታዘዝ የሚመለስ ጥያቄ አለ ፣ የእግዚአብሄርን ቃል በማሰላለስ የሚመለስ ጥያቄ አለ ፣ የእግዚአብሄርን ቃል በመናገር በማወጅ /ኮንፌስ/ በማድረግ የሚመለስ ጥያቄ አለ ፣ ሰውን በመውደድ የሚመለስ ጥያቄ አለ ፣ ሰውን ይቅር በማለት የሚመለስ ጥያቄ አለ ፣ ጌታን በማገልገል የሚመለስ ጥያቄ አለ ፣ በትግስት በመጠብቅ የሚመለስ ጥያቄ አለ ፣ ተግቶ በመስራት የሚመለስ ጥያቄ አለ፡፡ ለጥያቄ ሁሉ አንድ መልስ ብቻ እንዳለው ማሰብ ሞኝነት ነው፡፡
ስለዘህ ነው እግዚአብሄር ለምናልፍበት ነገር የሚያስፈልገውን ጥበብ እንዲሰጠን ዘወትር ልባችንን ለእርዳታ ወደ እግዚአብሄር ማንሳት ያለብን፡፡
ወንድሞቼ ሆይ፥ የእምነታችሁ መፈተን ትዕግሥትን እንዲያደርግላችሁ አውቃችሁ፥ ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቍጠሩት ትዕግሥትም ምንም የሚጎድላችሁ ሳይኖር ፍጹማንና ምሉዓን ትሆኑ ዘንድ ሥራውን ይፈጽም። ከእናንተ ግን ማንም ጥበብ ቢጎድለው፥ ሳይነቅፍ በልግስና ለሁሉ የሚሰጠውን እግዚአብሔርን ይለምን፥ ለእርሱም ይሰጠዋል። ያዕቆብ 1፡2-5
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ልዩልዩ #በልግስና #ብዙ #ጥበብ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ማስተዋል #እምነት #ፈተና #ፀሎት #ጌታ #የእግዚአብሄርቃል #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
በጥበብ መነገድ ይሻላል
በህይወት ስኬታማ የሚያደርገን ዋጋ የሚሰጠውን ነገር ዋጋ ስንሰጥና ቅድሚያ የሚሰጠውን ነገር ቅድሚያ ስንሰጥ ብቻ ነው፡፡ በህይወት በጣም የምንጓጓለት ነገር ሁሉ የሚያጓጓ እንዳይደለ የምናውቀው በጥበብ ነው፡፡ በህይወት ቅድሚያ የሚሰጠው ነገር ብለን የምናስበው ነገር ሁሉም ቅድሚያ እንደማይሰጠው የምናውቀው በጥበብ ነው፡፡ ጥበብ ጉልበታችንን ጊዜያችንን በማይሆን ነገር ላይ እንዳናባክን ያደርገናል፡፡
በህይወታችን ጉዳዬ የምንላቸው ብዙ ነገሮች ጉዳዬ የሚባሉ አይደሉም፡፡ በህይወት ጠቃሚ የሚመስሉን ነገሮች ሁሉ እንደምናስበው ጠቃሚ እንዳልሆኑ በጥበብ እናስተውላለን፡፡
ጥበብን የሚያገኝ ሰው ምስጉን ነው፥ ማስተዋልንም ገንዘቡ የሚያደርግ፤ በወርቅና በብር ከመነገድ ይልቅ በእርስዋ መነገድ ይሻላልና። ምሳሌ 3፡13-14
ጥበብን የሚያገኝ ሰው ምስጉን ነው፡፡ ጥበብን የሚያገኝ ሰው ተመራጭ ፣ ዕድለኛ ፣ ተጠቃሚ ፣ የታደለ ፣ የተመረጠ ፣ ደስተኛ ፣ የተባረከና የሚቀናበት ሰው ነው፡፡
በማስተዋል ሃብታም የሆነ ምስጉን ነው፡፡ ይበልጥ ማስተዋል ያለው ይበልጥ ባለጸጋ ነው፡፡
ምክኒያቱም በብር ሃብታም ከመሆን በጥበብ ሃብታም መሆን ይሻላል፡፡ በወርቅ ከመብዛት በጥበብ መብዛት ይሻላል፡፡ ጥበብ ከሚጎድልብን ገንዘብ ቢጎድልብን ይሻላል፡፡
ከእግዚአብሄር ጋር እንደሚገባ እንድትኖር የሚያደርግህ እግዚአብሄርን የመፍራት ጥበብ እንጂ ሃብት አይደለም፡፡
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ሰነፎች ግን ጥበብንና ተግሣጽን ይንቃሉ። ምሳሌ 1፡7
የህይወት ፈተና በገጠመህ ጊዜ ከፈተና የሚያስመልጥህ ሃብትህ ሳይሆን ጥበብ ነው፡፡
ወንድሞቼ ሆይ፥ የእምነታችሁ መፈተን ትዕግሥትን እንዲያደርግላችሁ አውቃችሁ፥ ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቍጠሩት ትዕግሥትም ምንም የሚጎድላችሁ ሳይኖር ፍጹማንና ምሉዓን ትሆኑ ዘንድ ሥራውን ይፈጽም። ከእናንተ ግን ማንም ጥበብ ቢጎድለው፥ ሳይነቅፍ በልግስና ለሁሉ የሚሰጠውን እግዚአብሔርን ይለምን፥ ለእርሱም ይሰጠዋል። ያዕቆብ 1፡2-5
ምንም ነገር ቢኖርህ ለምታስበው አላ ሁሉ አይበቃም፡፡ በህይወት ቅድሚያ የምትሰጠውና ቅድሚያ የማትሰጠው ነገር መኖር አለበት፡፡ ስለዚህ ጥበብ ከሌለህ ቅድሚያ መስጠት እንደምትችል አታውቅም፡፡
ብዙ የምንፈልጋቸው ነገሮች እንደምናስበው ያህል አያስፈልጉንም፡፡ ከዚያ ይበልጥ የሚየስፈልገን ጥበብ ነው፡፡ ብዙ የምንተማመንባቸው ነገሮች የህይወታችንን ጥያቄዎች አይፈቱም፡፡ አብዛኛው የህይወታችን ጥያቄዎች በዝና በገንዘብ በእውቀት አይመለሱም፡፡ ብዙ የህይወታቸን ጥያቄዎች የሚመለሱት በጥበብ ነው፡፡
ጥበብን የሚያገኝ ሰው ምስጉን ነው፥ ማስተዋልንም ገንዘቡ የሚያደርግ፤ በወርቅና በብር ከመነገድ ይልቅ በእርስዋ መነገድ ይሻላልና። ምሳሌ 3፡13-14
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ጥበብ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ማስተዋል #እምነት #ፈተና #ፀሎት #ጌታ #የእግዚአብሄርቃል #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
የእውነተኛ ምሁር ባህሪያት
-
- እውነተኛ ምሁር በእውቀቱ አይመካም
እውነተኛ ምሁር እውቀቱን ትልቅ ነገር አያደርገውም፡፡ እውነተኛ የተማረ ሰው እውቀት ስላለው ሌላ እውቀት የለሌለውን አይንቅም፡፡ እውነተኛ ምሁር ሌላውን በማክበሩና በትህትናው ይታወቃል፡፡ እውነተኛ ምሁር ሌሎችን በእውቀት እንዲያገለግል ስጦታ እንደተሰጠው አገልጋይ ራሱን ያያል፡፡
እነሆ፥ እግዚአብሔር ኃያል ነው፥ ማንንም አይንቅም እርሱም በማስተዋል ብርታት ኃያል ነው። ኢዮብ 36፡5
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ጠቢብ በጥበቡ አይመካ፥ ኃያልም በኃይሉ አይመካ፥ ባለ ጠጋም በብልጥግናው አይመካ፤ ኤርሚያስ 9፡23
- እውነተኛ ምሁር የትምህርትን ውስንነት ያውቃል፡፡
እውነተኛ ምሁር ሂሳብ ከተማረ ያልተማራቸው እጅግ ብዙ የትምህርት መስኮች እንዳሉ ይረዳል፡፡ እውነተኛ ምሁር ባልተማረበት ክፍል ራሱን አዋርዶ ከሌሎች ይማራል፡፡ እውነተኛ የተማረ ከእርሱ የተሻሉ እውቀት ያላቸው ሰዎች እንዳሉ ይረዳል፡፡
ማንም አንዳች የሚያውቅ ቢመስለው ሊያውቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም፤ 1ኛ ቆሮንቶስ 8፡2
- እውነተኛ ምሁር ቀለምነት ስጦታ እንጂ የትጋት ማረጋገጫ እንዳልሆነ ያውቃል
ሁሉ ሰው ቀለም እንዲሆን አልተጠራም፡፡ አንዳንዱ አርቲስት ሌላው ደግሞ የቴክኒክ ባለሙያ እዲሆን ተጠርቶዋል፡፡ እውነተኛ ምሁር የአእምሮ የትምህርት መያዝ ችሎታ የእግዚአብሄር ስጦታ እንጂ የትጋት ማረጋገጫ እንዳይደለ ያስባል፡፡ ከእርሱ የተሻለ የሚተጉ ሰዎች ያ የእውቀት መረዳት ችሎታው ስለሌላቸው የተማሩ እንዳይደሉ ያስባል፡፡
. . . የጥበብ መግዣ ገንዘብ መኖሩ ስለ ምንድር ነው? ጥበብን ይገዛ ዘንድ አእምሮ የለውምና።
- እውነተኛ ምሁር እውቀትን ለሌሎች ቀላል ያደርጋል፡፡
እውነተኛ ምሁር እርሱ ብቻ እንደተመረቀ ሌላው ደግሞ እንደማይመለከተው አያስብም፡፡ እውነተኛ ምሁር ስለሚያውቀው አውቀት በተራ ሰው ቋንቋ ይናገራል ያስረዳል፡፡ እውነተኛ ምሁር ነገሮችን በማቅለል እንጂ በወሳሰብ አይታወቅም፡፡
የመበለቶችን ቤት የሚበሉ ጸሎታቸውንም በማስረዘም የሚያመካኙ እነዚህ የባሰ ፍርድ ይቀበላሉ። ማርቆስ 12፡40
- እውነተኛ ምሁር የተማረውን ለማካፈል ይተጋል፡፡
እውነተኛ ምሁር እውቀቱን እጅግ የተቀደሰ ለጥቂት ሰዎች ብቻ የተለየ አያደርገውም፡፡ እውነተኛ የተማረ ትምህርቱን በሰዎች ውስጥ በማብዛት ይታወቃል፡፡ እውነተኛ የተማረ እውቀቱን በማካፈሉ የእርሱ ተፈላጊነት እንደሚጨምር እንጂ እንደሚቀንስ አያስብም፡፡ እውነተኛ ምሁር እውቀቱን በማካፈሉ ሌሎች ይበልጡኛል የሚል ስጋት የለውም፡፡ እውነተኛ ምሁር የሚኖረው በእውቀቱ ሳይሆን በእግዚአብሄር እንደሆነ ያስባል፡፡ እውነተኛ ምሁር ስኬቱ በእግዚአብሄ እንጂ በእውቀት እነዳይደለ ጠንቅቆ የሚረዳ ነው፡፡
እኔም ተመለስሁ፥ ከፀሐይ በታችም ሩጫ ለፈጣኖች፥ ሰልፍም ለኃያላን፥ እንጀራም ለጠቢባን፥ ባለጠግነትም ለአስተዋዮች፥ ሞገስም ለአዋቂዎች እንዳልሆነ አየሁ፤ ጊዜና እድል ግን ሁሉን ይገናኛቸዋል። መክብብ 9፡11
- እውነተኛ ምሁት አእምሮው ብቻ ሳይሆን ልቡም ሰፊ ነው፡፡ እውነተኛ ምሁር ሰዎችን ይወዳል፡፡ እውነተኛ ምሁር ከእርሱ የተለዩት ሰዎች የተሳቱ እንዳይደሉ ያውቃል፡፡ እውነተኛ ምሁር ከእርሱ ለተለዩት ሰዎች በልቡ ቦታ አለው፡፡
እግዚአብሔርም ለሰሎሞን እጅግ ብዙ ጥበብና ማስተዋል በባሕርም ዳር እንዳለ አሸዋ የልብ ስፋት ሰጠው። 1ኛ ነገስት 4፡29
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #እውቀት #ትምህርት #ቀለም #ምሁር #ስኬት #እረኛእግዚአብሄር #ስምረት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መፅሃፍቅዱስ #እውነተኛ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
ከዚህ ዘመን ይልቅ ያለፈው ዘመን ለምን ተሻለ?
በምድር ስንኖር ኑሮን አንድናቆምና እጅ እንድንሰጥ ሊያስፈሩን የሚመጡ ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ አንዳንድ ሰው ወጥቶ ህይወትን መጋፈጥ ሲፈራ ተኝቶ መዋል ያምረዋል፡፡ ሌላው ደግሞ ቶሎ ኢየሱስ እንደገና ተመልሶ ወይም እርሱ ወደ ሰማይ ሄዶ ችግርና መከራን ማምለጥ ይመኛል፡፡ ሰው በጌታ በኢየሱስ ያመነ ሰው ወደ ሰማይ የሚሄድበት ጊዜ አለው፡፡ ላሁን ግን የሚሰራ ስራ ስላለ በዚሁ ይቀመጣል፡፡
አንዳንዴ የሰዎችን ክፋት ስናይ ዘመኑ ያስፈራናል፡፡ እግዚአብሄር ግን የሚፈልገው በዚህ በእንግድነት አገር ታምነን እንድኖር ነው፡፡
በሰማይ የሚሸነፍ የምትቋቋመውቅ ጠላት ስለሌለ ማሸነፍ የሚባለውም ገድል የለም፡፡ ጌታ የሚፈልገው እዚሁ ጠላት ያለበት ኖረህ እንድታሸነፍ ነው፡፡ እዚሁ ጭለማ አህዛብን ድቅድቅ ጨለማ አህዛብን በሚሸፍንበት ምድር ነው ብርሃንህን ሊያወጣ የሚፈልገው፡፡ (ኢሳያስ 60፡1-2) እዚሁ በሞት ጥላ መካከል ነው አብሮህ መሆን የሚፈልገው፡፡ (መዝሙር 23፡4) እዚሁ በጠላቶችህ ፊት ለፊት ነው ራስህን በዘይት መቀባት የሚፈልገው፡፡ (መዝሙር 23፡3) እዚሁ ደረቁ ምድር ላይ መቶ እጥፍ እንድታፈራ የሚፈልገው፡፡ (ዘፍጥረት 26፡22) በምንም ነገር እጅ እንድትሰጥ ሳይሆን በጠበበው ደጅ ታግለህ እንድትገባ ነው የሚገፈልገው፡፡ (ማቴዎስ 7፡13) በትንሽ በትልቁ የሚያለቅስ ልፍስፍስ ሳይሆን ተናጣቂ ግፈኛ እንድትሆን ነው የሚፈልገው፡፡ (ማቴዎስ 11፡12)
ለዚህ ነው በምድር ተቀመጥ ታምነህ ተሰማራ ነው የሚለው፡፡
በእግዚአብሔር ታመን፥ መልካምንም አድርግ፥ በምድርም ተቀመጥ፥ ታምነህም ተሰማራ። መዝሙር 37፡3
ስለዚህ ነው የበፊቱን ያለፈውን ኑሮ አያሰብክ የወደፊቱ አይመርህ የሚለው፡፡ ምክኒያቱም እግዚአብሄር የሰጠህ ፀጋ ለዘመኑ ክፋት የሚበቃ ነው፡፡
እንደ ድሮ መንገድ ባይሆንም አሁንም ለጌታ የተሰጡ ሰዎች አሉ፡፡ እንደለመድከው ባይሆንም አሁንም ለጌታ መስዋእት የሚሆኑ ሰዎች አሉ፡፡ እንዳሰብከው ባይሆንም አሁንም ለጌታና ለጌታ ክብር ብቻ የሚኖሩ ሰዎች አሉ፡፡ እንደለመድነው ባይሆንም አሁንም ጌታን በሙሉ ልባቸው እያገለገሉ ያሉ ሰዎች አሉ፡፡
እግዚአብሄር በዘመናት መካከል አይለወጥም፡፡ ዘመን ሊለወጥ ዘመን ሊከፋ ይችላል ነገር ግን የማይለወጠው እግዚአብሄር ዘመኑን ለእኛ መልካምነት ይሰራዋል፡፡
ባለፈው ዘመን መልካም ያደረገው እግዚአብሄር እንደሞተ ሁሉ ያለፈው ዘመን ለምን የተሻለ አትበል፡፡
ከዚህ ዘመን ይልቅ ያለፈው ዘመን ለምን ተሻለ? ብለህ አትናገር፤ የዚህን ነገር በጥበብ አትጠይቅምና። መክብብ 7፡9-10
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ስብከት #መዳን #ዘመን #እምነት #ወንጌል #ማኅበረተኛ #ስብከት #ቃል #ዝራ #የምድርጨው #የአለምብርሃን #ተነሺ #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
አያዋጣም
በንግድ አንድን እቃ ሸጠን የምናገኘውን ገንዘብ ብቻ አይተን ያዋጣል ማለት አንችልም፡፡ የአንድን ነገር አዋጪነቱን ለማወቅ አንድን ነገር የሸጥንበትን ዋጋ ብቻ ሳይሆን የገዛንበትን ዋጋም ከግምት ውስጥ እናስገባዋለን፡፡ ምንም በውድ ዋጋ ቢሸጥ በውድ ዋጋ የተገዛ ከሆነና ትርፉን እጅግ የሚቀንስ ከሆነ አዋጭ አይደለም እንላለን፡፡ እንደ ነጋዴ አዋጪ ያልሆነን ነገር ለመሸጥ ፍላጎት አይኖረንም፡፡
በህይወታችን ጊዜያችንን ፣ ጉልበታችንንና እውቀታችንን የምናፈስባቸው ነገሮች ብዙን ጊዜ ውጤት ያመጣሉ፡፡ ነገር ግን የምንከፍለው ዋጋ ከምናገኘው ውጤት ከበለጠ ወይም እኩል ከሆነ አዋጭ አይደለም፡፡ አንዳንድ የምናደርጋቸው ነገሮች በእርግጥ ይከናወናሉ ነገር ግን ካወጣነው ጉልበት አንፃር አዋጪ አይደሉም፡፡ በጥበብ ነው ያደረግነው አዋጪ ነው የሚባለው ነገር የምንከፍለው ዋጋ ሲያንስ የምናገኘው ሲበዛ ነው፡፡
በክርስትናም እንዲሁ ነው፡፡ አንዳንድ ነገሮች ጥሩ ናቸው ነገር ግን ከፍተኛ ጥቅም አይሰጡንም፡፡ አንዳንድ ነገሮች አይጎዱም ነገር ግን ከፍተኛን ጥቅም አይሰጡም፡፡ በክርስትና አዋጪ ስለሆኑ የጥበብ ውሳኔዎች እንመልከት፡፡
አዋጪነቱን የተረዳ ብልሃተኛ ሰው ነፍሱን አይዝም በጌታ ላይ ይጥላል፡፡ አዋጪነቱን የተረዳ ሰው የእግዚአብሄርን ቃል ታዞ ከነፍሱ ድምፅ በላይ የጌታን ድምፅ ይሰማል ይታዘዛል፡፡ አዋጪነቱን የተረዳ ሰው
ነፍሱን ሊያድን የሚወድ ሁሉ ያጠፋታል፤ ስለ እኔ ግን ነፍሱን የሚያጠፋ ሁሉ ያገኛታል። ማቴዎስ 16፡25
አዋጪነቱን የተረዳ ብልሃተኛ ብልሃተኛ አናፂ ዋጋ መክፈል በሚገባው በጥራት ላይ ዋጋ ይከፍላል፡፡
ጥበበኛ ሰው ዋጋ በሚያስከፍል እውነተኛ ነገር ላይ በደስታ ዋጋ ይከፍላል፡፡ አሁን ዋጋ የከፈለበት ነገር ነገ በብዙ እጥፍ ይጠቅመዋል፡፡ ብልሃተኛ አናፂ ለትክለክለኛ ነገር ዋጋ ይከፍላል፡፡ ትክክለኛ አናፂ ቤቱን ቶሎ ሰርቶ መጨረሱን ብቻ ሳይሆን ቤቱ በትክክለኛ ነገር መሰራቱን ያረጋግጣል፡፡ ትክክለኛ አናፂ ገንብቶ ለመጨረስ አይቸኩልም ነገር ግን በሚቆይ በሚበረክትና ዘላቂ ነገር ላይ ዋጋ ለመክፈል ይታገሳል፡፡
ማንም ግን በዚህ መሠረት ላይ በወርቅ ቢሆን በብርም በከበረ ድንጋይም በእንጨትም በሣርም ወይም በአገዳ ቢያንጽ፥ የእያንዳንዱ ሥራ ይገለጣል፤ በእሳት ስለሚገለጥ ያ ቀን ያሳያልና፥ የእያንዳንዱም ሥራ እንዴት መሆኑን እሳቱ ይፈትነዋል። ማንም በእርሱ ላይ ያነጸው ሥራ ቢጸናለት ደመወዙን ይቀበላል፤ የማንም ሥራ የተቃጠለበት ቢሆን ይጎዳበታል፥ እርሱ ራሱ ግን ይድናል ነገር ግን በእሳት እንደሚድን ይሆናል። 1ኛ ቆሮንቶስ ሰዎች 3፡12-15
አዋጪነቱን የተረዳ ብልሃተኛ ሰው የጊዜው መከራ በመታገስ የሚበልጠውን ክብር ይጠብቃል፡፡
ሰው ማለፍ ያለበትን የጊዜውን መከራ በራሱ መንገድ ለመሸወድ ቢሞክር አያዋጣም፡፡ ሰው በራሱ መንገድ ከእግዚአብሄር ሃሳብ ወጥቶ ማለፍ ያለበትን መከራ ሊሸውደው ይችላል፡፡ ይህ ግን ትርፉና ኪሳራው ሲታይ አዋጪ አይደለም፡፡ የሚያዋጣው ከሚመጣው ክብር ጋር ሲመዛዘን ቀላል የሆነውን የጊዜውን ስቃይ መታገስ ነው፡፡
የማይታየውን እንጂ የሚታየውን ባንመለከት፥ ቀላል የሆነ የጊዜው መከራችን የክብርን የዘላለም ብዛት ከሁሉ መጠን ይልቅ ያደርግልናልና፤ የሚታየው የጊዜው ነውና፥ የማይታየው ግን የዘላለም ነው። 2ኛ ቆሮንቶስ 4፡17-18
ለእኛም ይገለጥ ዘንድ ካለው ክብር ጋር ቢመዛዘን የአሁኑ ዘመን ሥቃይ ምንም እንዳይደለ አስባለሁ። ሮሜ 8፡18
አዋጪነቱን የተረዳ ብልሃተኛ ሰባኪ የሰዎችን እምነት በእግዚአብሄር ሃይል ላይ እንዲሆን ዋጋ ይከፍላል፡፡
ጠቢብ ሰባኪ ህይወቱን በንግግር ብልጫ ላይ ሳይሆን በእግዚአብሄር ቃልና ሃይል ላይ ይመሰርታል፡፡ ጠቢብ ሰው በእምነት እንጂ በብልጣብልጥነት አይኖርም፡፡ ጠቢብ ሰባኪ የሚሰሙትን ለእምነት ኑሮ እንጂ ለብልጣብልጥነት ምሳሌ አይሆናቸውም፡፡ ጠቢብ ሰባኪ ሰዎች በእግዚአብሄር ቃል ጥበብ ላይ እንጂ በሰው ጥበብ ላይ እንዲታመኑ አያደርጋቸውም፡፡ ሰው ካገለገለና ከሰበከ ላይቀር እውነተኛውን ነገር ሰብኮ እውነተኛውን ነገር ኖሮ ህይወቱን ቢያሳልፍ ብቻ አዋጪ ነው፡፡
እኔም፥ ወንድሞች ሆይ፥ ወደ እናንተ በመጣሁ ጊዜ በቃልና በጥበብ ብልጫ ለእግዚአብሔር ምስክርነቴን ለእናንተ እየነገርሁ አልመጣሁም። እምነታችሁም በእግዚአብሔር ኃይል እንጂ በሰው ጥበብ እንዳይሆን፥ ቃሌም ስብከቴም መንፈስንና ኃይልን በመግለጥ ነበረ እንጂ፥ በሚያባብል በጥበብ ቃል አልነበረም። 1ኛ ቆሮንቶስ 2፡1፣4-5
አዋጪነቱን የተረዳ ብልሃተኛ ኢንቨስተር በሰው ልጆች መዳን ላይ ገንዘቡን ያፈሳል፡፡
አዋጪነቱን የተረዳ ባለገንዘብ በምድር ላይ የሚቀር ጊዜያዊ ነገርን ሲሰራ አይኖርም፡፡ አዋጪነቱን የተረዳ ሰው ገንዘቡን ዘላለማዊ ዋጋ ያለው ነገር ላይ ያጠፋል፡፡ አዋጪነቱን የተረዳ ሰው የሰው ልጆችን ወደ መግስተ ሰማያት እንዲሄዱ በመርዳት የላቀ ዋጋ ያለው የሰዎች መዳን ላይ ያውለዋል፡፡ አዋጭነቱን የተረዳ ሰው ብዙዎችን ለመታደግ የሚውለውን ሃብቱን ሁሉ በራሱ ላይ ብቻ አውሎ እየጨርሰውም፡፡
እኔም እላችኋለሁ፥ የዓመፃ ገንዘብ ሲያልቅ በዘላለም ቤቶች እንዲቀበሉአችሁ፥ በእርሱ ወዳጆችን ለራሳችሁ አድርጉ። ሉቃስ 16፡9
ብልና ዝገት በሚያጠፉት ሌቦችም ቆፍረው በሚሠርቁት ዘንድ ለእናንተ በምድር ላይ መዝገብ አትሰብስቡ፤ ነገር ግን ብልም ዝገትም በማያጠፉት ሌቦችም ቆፍረው በማይሠርቁት ዘንድ ለእናንተ በሰማይ መዝገብ ሰብስቡ፤ መዝገብህ ባለበት ልብህ ደግሞ በዚያ ይሆናልና። ማቴዎስ 6፡19-21
አዋጪነቱን የተረዳ ብልሃተኛ ባለጠጋ በገንዘብ ብቻ ሳይሆን ለእውነተኛ ህይወት በመልካም ስራ ባለጠጋ ይሆናል፡፡
አዋጪነቱን የተረዳ ባለጠጋ ባለጠግነት ግብ እንዳልሆነ ይረዳል፡፡ ባለጠግነት የመልካም ስራ ባለጠግነት የመጀመሪያ ደተረጃ እንጂ የመጨረሻው ደረጃ እነዳልሆነ ይረዳል፡፡ የገባው ባለጠጋ ባለጠግነቱ ታማኝነቱ የሚፈተንበት መልካም አጋጣሚ ብቻ እንደሆነ ይረዳል፡፡ የገባው ባለጠጋ በገንዘብ ባለጠግነቱ ልክ የመልካም ባለጠጋ ለመሆን ይተጋል፡፡ የገባው የገንዘብ ባለጠጋ የገንዘቡን ባለጠግነት ወደ እውነተኛ የመልካም ስራ ባለጠግነት ይለውጠዋል፡፡
እውነተኛውን ሕይወት ይይዙ ዘንድ፥ ለሚመጣው ዘመን ለራሳቸው መልካም መሠረት የሚሆንላቸውን መዝገብ እየሰበሰቡ፥ መልካምን እንዲያደርጉ በበጎም ሥራ ባለ ጠጎች እንዲሆኑ፥ ሊረዱና ሊያካፍሉም የተዘጋጁ እንዲሆኑ ምከራቸው። 1ኛ ጢሞቴዎስ 6፡18-19
አዋጪነቱን የተረዳ ብልሃተኛ ሰው አለሙን ሁሉ አትርፎ ነፍሱን ማጉደል አይፈልግም፡፡
አዋጪነቱን የተረዳ ብልሃተኛ ሰው አለሙን ሁሉ አጥቶ ነፍሱን ቢያጎድል ይመርጣል፡፡
ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል? ወይስ ሰው ስለ ነፍሱ ቤዛ ምን ይሰጣል? ማቴዎስ 16፡26
አዋጪነቱን የተረዳ ብልሃተኛ ሰው ስሜቱን ይገዛል እንጂ የከበረውን ብኩርናውን በጊዜያዊ ጥቅም አይለውጠውም፡፡
ወይም ስለ አንድ መብል በኵርነቱን እንደ ሸጠ እንደ ዔሳው ለዚህ ዓለም የሚመች ሰው እንዳይሆን ተጠንቀቁ። ዕብራውያን 12፡16
አዋጪነቱን የተረዳ ብልሃተኛ ሰው በታማኝነት ይጠብቃል እንጂ መሰረት ለሌላት ፈጥና ለምትከማች ሃብት አይጓጓም አላስፈላጊ ዋጋም አይከፍልም፡፡
በችኰላ የምትከማች ሀብት ትጐድላለች፤ ጥቂት በጥቂት የተከማቸች ግን ትበዛለች። ምሳሌ 13፡11
የታመነ ሰው እጅግ ይባረካል፤ ባለጠጋ ለመሆን የሚቸኵል ግን ሳይቀጣ አይቀርም። ምሳሌ 28፡20
አዋጪነቱን የተረዳ ብልሃተኛ ሰው እግዚአብሄር እንዲያከብረው ቀድሞ ራሱን ያዋርዳል፡፡
ራስን ማክበር ከንቱ ድካምና ንፋስን እንደ መከተል መሆኑን የተረዳ ሰው ራሱን ለማክበር ሲሯሯጥ አይታይም፡፡ ራስን ማክበር ወጭው ብዙ ገቢው ግን ጥቂት መሆኑን የተረዳ ሰው እራሱን ለማክበር መውጣት መውረዱን ትቶ እግዚአብሄር እንዲያከብረው ለእግዚአብሄር ጊዜ ይሰጣል፡፡ አዋጭነቱን የተረዳ ሰው እግዚአብሄር ያልሰጠውን ክብር እጁን ተንጠራርቶ እራሱ እይወስድም እግዚአብሄር እስኪሰጠው የእግዚአብሄርን ጊዜ በትግስት ይጠብቃል፡፡
እንዲሁም፥ ጐበዞች ሆይ፥ ለሽማግሌዎች ተገዙ፤ ሁላችሁም እርስ በርሳችሁ እየተዋረዳችሁ ትሕትናን እንደ ልብስ ታጠቁ፥ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማልና፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል። እንግዲህ በጊዜው ከፍ እንዲያደርጋችሁ ከኃይለኛው ከእግዚአብሔር እጅ በታች ራሳችሁን አዋርዱ፤ 1ኛ ጴጥሮስ 5፡5-6
አዋጪነቱን የተረዳ ብልሃተኛ ሰው ይባርካል በረከትን ይወርሳል እንጂ ማንንም አይረግምም፡፡
ክፉን በክፉ ፈንታ ወይም ስድብን በስድብ ፈንታ አትመልሱ በዚህ ፈንታ ባርኩ እንጂ፥ በረከትን ልትወርሱ ለዚህ ተጠርታችኋልና። ሕይወትን ሊወድ መልካሞችንም ቀኖች ሊያይ የሚፈልግ ሰው፥ መላሱን ከክፉ ከንፈሮቹንም ተንኰልን ከመናገር ይከልክል፤ ከክፉ ፈቀቅ ይበል፥ መልካምንም ያድርግ፥ ሰላምን ይሻ ይከተለውም፤ 1ኛ ጴጥሮስ 3፡9
አዋጪነቱን የተረዳ ብልሃተኛ ሰው ራሱን ለመንፈሳዊ ነገር ያስለምዳል፡፡
ሰውነትን ለሥጋዊ ነገር ማስለመድ ለጥቂት ይጠቅማልና፤ እግዚአብሔርን መምሰል ግን የአሁንና የሚመጣው ሕይወት ተስፋ ስላለው፥ ለነገር ሁሉ ይጠቅማል። 1ኛ ጢሞቴዎስ 4፡8
አዋጪነቱን የተረዳ ብልሃተኛ ሰው ለዘላለም በሚኖረው በቃሉ ለመኖር የሚከፈለውን ዋጋ ሁሉ ይከፍላል፡፡
አዋጭነቱ የተረዳ ሰው ከእግዚአብሄር ቃል ውጭ ያለን ማንኛውንም ነገር ላለማድረግና ህይወቱን ላለማባከን ይሳሳል፡፡ አዋጭነቱን የተረዳ ሰው አስቸጋሪ ቢሆን እንኳን ለእግዚአብሄር ቃል ዋጋን በደስታ ይከፍላል፡፡ አዋጭነቱን የተረዳ ሰው ምንም ወደታች ቢያስወርደውና ቢያስቆፍረውም በቃሉ የተመሰረተ አስተማማኝ ህይወትን ለመገንባት ይተጋል፡፡
ወደ እኔ የሚመጣ ሁሉ ቃሌንም ሰምቶ የሚያደርገው፥ ማንን እንዲመስል አሳያችኋለሁ። ቤት ሲሠራ አጥልቆ የቆፈረ በዓለት ላይም የመሠረተ ሰውን ይመስላል፤ ጐርፍም በመጣ ጊዜ ወንዙ ያን ቤት ገፋው፥ በዓለት ላይም ስለ ተመሠረተ ሊያናውጠው አልቻለም። ሰምቶ የማያደርገው ግን ያለ መሠረት በምድር ላይ ቤቱን የሠራ ሰውን ይመስላል፤ ወንዙም ገፋው ወዲያውም ወደቀ የዚያ ቤት አወዳደቅም ታላቅ ሆነ። ሉቃስ 6፡47-49
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ራእይ #መዳን #እምነት #አንድነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ህብረት #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #የዘላለምህይወት #ፅናት #ትግስት #መሪ
የእውቀት ማጣት አምስቱ ምልክቶች
እውቀት ብርሃን ነው፡፡ ሰው የእግዚአብሄር ቃል እውቀት ከሌላው ነገር ሁሉ ይጨላልምበታል፡፡ ሰው ትክክለኛው የመፀሃፍ ቅዱስ እውቀት ከሌላው ኑሮው በሙከራና በውድቀት የተሞላ ይሆናል፡፡
ሰው በእግዚአብሄር ቃል እውቀት ሲሞላ የእግዚአብሄርን መንግስት በደስታ ማገልገል ይችላል፡፡ ሰው በእግዚአብሄር ቃል እውቀት ሲሞላ ነገሮችን እንደ አመጣጣቸው መያዝ እና ማስተናገድ ይችላል፡፡ ሰው በእግዚአብሄር እውቀት ሲሞላ ሁኔታዎችን ሁሉ በማስተዋል ተጋፍጦ ከነገሮች በላይ አሸናፊ ይሆናል፡፡
ሰው የቃሉ እውቀት ከሌላው ቅድሚያ መስጠትን አያውቅም፡፡
የህይወት ስኬት የሚለካው በህይወት ቅድሚያ መስጠትን በማወቅ ላይ ነው፡፡ ለምን ቅድሚያ መስጠት እንዳለብን ካወቅንና የህይወት ሃላፊነቶችን ሁሉ በቦታ በቦታቸው ካስቀመጥናቸው አሸናፊ መሆን እንችላለን፡፡ የእግዚአብሄር ቃል እውቀት የሌለው ሰው ግን የቱን ከየቱ እንደሚያደርገው ስለማያውቅ ሃይሉን በማይገባ ጥቃቅን ነገር ላይ ያባክንና ሃይሉን ማጥፋት ባለበት ነገር ላይ የሚገባውን ሳያደርግ ይቀራል፡፡
እንግዲህ፦ ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤ ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል። ማቴዎስ 6፡31-33
እውቀት የሌለው ሰው ለምን እንደተጠራ አያውቅም፡፡
እውቀት የሌለው ሰው እግዚአብሄር ለምን እንደጠራው ስለማይረዳ ሁሉም ውስጥ በመግባት ጉልበሩን ሲጨርስ ይኖራል፡፡ የሰው ጉልበት ውስን ነው፡፡ ሰው ሁሉንም ነገር ለማድረግ ከሞከረ ምንም ነገር ሳያደርግ ይቀራል፡፡ የቃሉ አውቀት የሚያስፈልገው እግዚአብሄር ለምን እንደጠራን እንድናውቅ ነው፡፡ ለምን እንደተጠራ የሚያውቅ ሰው በአትኩሮት የህይወት ሩጫን በሚገባ መሮጥ እና መፈፀም ይችላል፡፡ ለምን እንደተጠራ የሚያውቅ ሰው ግቡን እስኪመታ አያርፍም፡፡ የቃሉ እውቀት ያለው ሰው አላማውን ከግብ ሲያደርሷ ያርፋል በህይወቱም ይደሰታል፡፡
የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ። ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን . . . ታውቁ ዘንድ ነው፤ ኤፌሶን 1፡17-19
መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 4፡7
እውቀት የጎደለው ሰው በእግዚአብሄር ፊት ያለውን የክብር ደረጃ አይረዳም፡፡
በእግዚአብሄር ያለንን ቦታ ማወቃችን ካለፉክክር ሌሎችን እንድናገለግል ይረዳናል፡፡ በእግዚአብሄር ዘንድ ያለውን ቦታ ያልተረዳ ሰው እግዚአብሄር አክብሮት እያለ ቦታውን ከፍ ለማድርግ ህይወቱን በከንቱ ይፈጃል፡፡ በእግዚአብሄር ያለውን የክብር ቦታ የማያውቅ ሰው ማንንም ማገልገል ሳይችል በምስኪንነት አስተሳሰብ ራሱን ብቻ በማገልገል ላይ ተጠምዶ ራሱን ያባክናል፡፡ ኢየሱስ በምድር ላይ ትሁት ሆኖ ለእግዚአብሄር አብ እስከሞት ድረስ በሚገባ እንዲታዘዝ ያደረገው ማንነቱን ማወቁ ነው፡፡
ኢየሱስ አብ ሁሉን በልጁ እንደ ሰጠው ከእግዚአብሔርም እንደ ወጣ ወደ እግዚአብሔርም እንዲሄድ አውቆ፥ ከእራት ተነሣ ልብሱንም አኖረ፥ ማበሻም ጨርቅ ወስዶ ታጠቀ፤ ዮሃንስ 13፡3-4
እውቀት የጎደለው ሃብታም ሰው ሃብታም ለመሆን በከንቱ ይጥራል፡፡
እውቀት የሌላው ሰው በሁሉ ባለጠጋ ተደርጎ ሳለ ሃብታም ለመሆን በሚደረግ ጥረት በአልባሌ ነገር ህይወቱን ይፈጃል፡፡ ስለ እረኛው በቂ እውቀት የሌለው ሰው ያጣው ነገር እንዳለ ስለሚሰማው ያንን ነገር ለማሟላት እግዚአብሄር የሰጠውን የህይወት ሃላፊነት ይተዋል፡፡ እውቀት የጎደለው ሰው ያለውን የርስት ክብር ስለማይረዳ የሚያልፍ የምድር ርስት ለማከማቸት ቅድሚያ በመስጠት ህይወቱን ያባክናል፡፡
የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ። ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ . . . በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን . . . ታውቁ ዘንድ ነው፤ ኤፌሶን 1፡17-19
እውቀት የጎደለው ሰው በተሰጠው ሃይል መጠቀም ያቅተዋል፡፡
ኢየሱስን አዳኙ አድርጎ የተቀበለ ሰው ሁሉ የእግዚአብሄር ታላቅ ሃይል በውስጡ ይኖራል፡፡ ሰው ግን በውስጡ ያለውን ሃይል ካልተረዳ በድካምና በሽንፈት ሊኖር ይችላል፡፡ እግዚአብሄር የሁሉ አሸናፊ አድርጎት እያለ ካላወቀ በሁሉ ተሸንፎ ይኖራል፡፡
የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ። ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ . . . ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው፤ ኤፌሶን 1፡17-19
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#እውቀት #ጥበብ #ነፍስ #መዳን #ኢየሱስ #ጌታ #እግዚአብሔር #እውቀት #ቅድሚያ #መታዘዝ #ርስት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ባለጠግነት #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ሃይል #ጥሪ #ክብር #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #አእምሮ #ሰላም #ማስተዋል #ልጅ
ልዩ ልዩ የእግዚአብሔር ጥበብ
ብዙ ልዩ ልዩ የእግዚአብሔር ጥበብ አሁን በቤተ ክርስቲያን በኩል በሰማያዊ ስፍራ ውስጥ ላሉት አለቆችና ሥልጣናት ትታወቅ ዘንድ፤ ኤፌሶን 3፡10
የምድር ችግር ዘርፈ ብዙ ነው፡፡ የሰይጣን ማጥቂያውም መንገድ ብዙ ነው፡፡ ስለዚህ ዘርፈ ብዙ ለሆነ ችግር ቀላል መልስ የለውም፡፡ ዘርፈ ብዙ ለሆነ የጠላት ጥቃት አንድ መከላከያ የለውም፡፡
ጠላትን ባለን ነገር ሁሉ ነው የምንቋቋመው፡፡
እግዚአብሄርም ለጠላት ዘርፈ ብዙ ማታለል መድሃኒት የሆነውን ዘርፈ ብዙ ጥበብ ሰጥቶናል፡፡
በብሉይ ኪዳንም እንዲህ ተብሎ ተፅፏል፡፡
ከአዛሄልም ሰይፍ ያመለጠውን ሁሉ። ኢዩ ይገድለዋል፤ ከኢዩም ሰይፍ ያመለጠውን ሁሉ ኤልሳዕ ይገድለዋል። 1ኛ ነገሥት 19፡17
ጠላትን ድል የምንነሳው በአምልኮም ነው ፣ በእምነት እወጃም ነው ፣ በፀሎትም ነው ፣ በትእግስትም ነው ፣ በትጋትም ነው ፣ በመጠበቅም ነው ፣ በፀጥታም ነው ፣ በአንድነትም ነው ፣ በምስጋናም ነው ፣ በመንፈስ በመመራትም ነው ፣ በመስጠትም ነው ፣ በጥበብም ነው ፣ በይቅርታም ነው፡፡
ስለዚህ ነው አውቃለሁ ማለት የሌለብን ፣ ስለዚህ ነው በቀጣይነት የእግዚአብሄን ጥበብ ከእግዚአብሄር ቃል ውስጥ መፈለግ ያለብን ፣ ስለዚህ ነው በቀጣይነት የእግዚአብሄን ፊት መፈለግ ያለብን፡፡
ብዙ ልዩ ልዩ የእግዚአብሔር ጥበብ አሁን በቤተ ክርስቲያን በኩል በሰማያዊ ስፍራ ውስጥ ላሉት አለቆችና ሥልጣናት ትታወቅ ዘንድ፤ ኤፌሶን 3፡10
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ጥበብ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ማስተዋል #እምነት #ፈተና #ፀሎት #ጌታ #የእግዚአብሄርቃል #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
የጥበብ መጀመሪያ ምንጭ
ሰው የተፈጠረው ለእግዚአብሄር ክብር ነው፡፡ የሰው መረዳት ዝቅተኛው መመዘኛ እግዚአብሄርን መፍራቱ ነው፡፡ የሰው መረዳት የሚጀምረው ከእግዚአብሄር ጋር እንዴት እንደሚኖር በማወቁ ነው፡፡ የሰው እውቀቱ የሚለካው በትንሹ ለእግዚአብሄር አምላክነት እውቅና መስጠቱ በማወቁ ነው፡፡ የሰው እውቀቱ የሚታየው ከእግዚአብሄር ከፈጣሪው ጋር ያለውን ግንኙነት በመረዳቱ ነው፡፡
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ምሳሌ 1፡7
ሰው እጅግ የተዋጣለት የጠፈር ተመራማሪ ቢሆን ከእግዚአብሄር ጋር ግን እንዴት እንደሚኖር ካላወቀ ምንም አያውቅም፡፡ ሰው በሌላ በብዙ ነገር የተሳካለት አዋቂ ሆኖ ለፈጠረው ለእግዚአብሄር እውቅና መስጠት ካላወቀ ሀ ሁ አልቆጠረም ማለት ነው፡፡ ሰው በሌላ ነገር የተካነ ሆኖ ለክብሩ ከፈጠረው ከእግዚአብሄር ጋር ስላለው ግንኙነት መረዳቱ ከሌለው ምንም አያውቅም ማለት ነው፡፡ ሰው ምንም ቢያውቅ ለእግዚአብሄር ፈጣሪነትና ባለቤትነት እውቅና ካለሰጠ የእውቀት መጀመሪያ ላይ አልደረሰም ማለት ነው፡፡
እግዚአብሄን መፍራት ግን ከድርጊት አይጀመርም፡፡ በድርጊታችን እግዚአብሄርን ለመፍራት መፍጨርጨር የለብንም፡፡ በድርጊታችን አግዚአብሄርን ለመፍራት የድርጊታችንን ምንጩን ማስተካከል ይኖርብናል፡፡ በንግግራችን እና በድርጊታችን እግዚአብሄርን ለመፍራት ንግግራችንና ድርጊታችን የሚመጣበትን ምንጩ አስተሳሰባችንን ማስተካከል ይኖርብናል፡፡
መጽፅሃፍ ቅዱስ የማንኛውም ድርጊት ምንጩ ሃሳብ እንደሆነ ያስተምረናል፡፡ እንዲያውም ሰው በልቡ እንደሚያስበው እንደዚሁ እንደሆነ መፅሃፍ ያስተምረናል፡፡ በአስተሳሰብ ህይወቱ እግዚአንብሄርን የሚፈራ ሰው በንግግሩ እግዚአብሄርን ይፈራል፡፡ በአስተሳሰቡ እግዚአብሄርን የሚፈራ በራሱ በድርጊቱ እግዚአብሄርን ይፈራል፡፡
በልቡ እንዳሰበ እንዲሁ ነውና፤ ምሳሌ 23፡7
ስለዚህ ነው ኢየሱስ ፈሪሳዊያንን እናንተን የሚያረክሳችሁ ድርጊት ሳይሆን የልባችሁ ሃሳብ ነው እያለ የሚወቅሳቸው፡፡
ከአፍ የሚወጣ ግን ከልብ ይወጣል፥ ሰውንም የሚያረክሰው ያ ነው። ከልብ ክፉ አሳብ፥ መግደል፥ ምንዝርነት፥ ዝሙት፥ መስረቅ፥ በውሸት መመስከር፥ ስድብ ይወጣልና። ማቴዎስ 15፡18-19
ሰው እግዚአብሄርን በእውነት የሚፈራው በሃሳብ ደረጃ ነው፡፡ ሰው በሃሳብ ደረጃ እግዚአብሄርን ከፈራ ከመቀፅበት በንግግርም ሆነ በድርጊት እግዚአብሄርን የመፍራት ህይወት ይኖረዋል፡፡ ሰው ግን በአስተሳሰብ ህይወቱ እግዚአብሄርን ካልፈራና ስርአት አልባ ከሆነ በድርጊቱ እግዚአብሄን መፍራት አይችልም፡፡ ሰው ሰው አያየኝም ብሎ ክፉን ቢያስብ በንግግሩና በድርጊቱ ሰው ያየዋል፡፡
ጌታም እንዲህ አለው፦ አሁን እናንተ ፈሪሳውያን የጽዋውንና የወጭቱን ውጭ ታጠራላችሁ፥ ውስጣችሁ ግን ቅሚያና ክፋት ሞልቶበታል፡፡ ሉቃስ 11፡39
ስለዚህ በአስተሳሰባችን እግዚአብሄርን በመፍራት እግዚአብሄርን የመፍራት ህይወት ይኑረን፡፡
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ምሳሌ 1፡7
ፀሎት
እግዚአብሄር ሆይ በአስተሳሰቤ አንተን እፈራለሁ፡፡ እግዚአብሄር ሆይ ወደ አእምሮዬ የመጣውን ሃሳብ ሁሉ አላስብም፡፡ እግዚአብሄር ሆይ የማስበውን ማንኛውንም ሃሳብ አንተን በመፍራት አስባለሁ፡፡ እግዚአብሄ ሆይ እንደቃልህ ያልሆነን ሃሳብ ከአእምሮዬ አሽቀንጥሬ እጥላለሁ፡፡ አንደ ቃልህ ያልሆነውን ሃሳብ በአእምሮዬ አላስተናገድም፡፡ እግዚአብሄር ሆይ በአስተሳሰብ ህይወቴ አንተን በመፍራት ወዳዘጋጀህልኝ በረከት ውስጥ እገባለሁ፡፡ ስላስተማርከኝ አመሰግናለሁ፡፡ በኢየሱስ ስም ፡፡ አሜን
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #ሃሳብ #አእምሮ #ልብ #እግዚአብሔርንመፍራት #ጥበብ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #እምነት #ቃል #ማደስ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
የብዙ ጥያቄ መልስ
ጥበብን ማግኘት ምንኛ ከወርቅ ይሻላል! ማስተዋልንም ማግኘት ከብር ይልቅ የሚመረጥ ነው። ምሳሌ 16፡16
ጥበብን የሚያገኝ ሰው ምስጉን ነው፥ ማስተዋልንም ገንዘቡ የሚያደርግ፤ በወርቅና በብር ከመነገድ ይልቅ በእርስዋ መነገድ ይሻላልና። ምሳሌ 3፡14
በህይወት የብዙ ጥያቄያችንን መልስ የምንፈልገው በተሳተ ቦታ ነው፡፡ በተለይ ወርቅና ብር ውስጥ የህይወት ጥያቄያችን ሁሉ መልስ ያለ ይመስለናል፡፡ ተጨማሪ ገንዘብ ባገኝ የህይወት ጥያቄዬ ይመለሳል ብለን እናስባለን፡፡ ለምሳሌ በህይወት ያሉብንን ተግዳሮቶች ለማለፍ ብዙ ጊዜ የሚያስፈልገን ቁልፍ ተጨማሪ ገንዘብ ሳይሆን ተጨማሪ ጥበብ ነው፡፡
ጥበብ ያለንን ነገር እንዴት በሚገባ እንደምንጠቀምበት ያስተምረናል፡፡ ጥበብ ምን ማደርግ እንዳለብን በማናውቅ ጊዜና ህይወት ፈተና ሲሆንብን ምን ማድረግ እንዳለብን መንገዱን ያሳየናል፡፡ ስለዚያ ነው በፈተና የሚያልፍ ሰው ጥበብ ይለምን እንጂ ይበለጥ ገንዘብ ይለምን የማይለው፡፡ በጥበብ የማይፈታ ችግር የማናልፈው ፈተና የለም፡፡ በእግዚአብሄር ጥበብ በእግዚአብሄር እይታ ካየነው ሊፈታ የማይቻል ነገር የለም፡፡
ወንድሞቼ ሆይ፥ የእምነታችሁ መፈተን ትዕግሥትን እንዲያደርግላችሁ አውቃችሁ፥ ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቍጠሩት ትዕግሥትም ምንም የሚጎድላችሁ ሳይኖር ፍጹማንና ምሉዓን ትሆኑ ዘንድ ሥራውን ይፈጽም። ከእናንተ ግን ማንም ጥበብ ቢጎድለው፥ ሳይነቅፍ በልግስና ለሁሉ የሚሰጠውን እግዚአብሔርን ይለምን፥ ለእርሱም ይሰጠዋል። ያዕቆብ 1፡2-5
እኩል ገንዘብ ያላቸውን ሁለት ሰዎች የሚለየው ጥበባቸው ነው፡፡ አንዱ እንዴት በጥበብ እንደሚያስተዳድርው ያውቃል ሌላው ደግሞ ጥበብ ይጎድለዋል፡፡ ሰው ደግሞ ምንም ነገር ቢኖረው እንዴት እንደሚያስተዳድረው ጥበቡ ከሌለው እንደሌለው ይቆጠራል፡፡ ስለዚህ ነው መፅሃፍ ቅዱስ ከሃብት ሁሉ በላይ ማስተዋልን እንድናተርፍ የሚያስተምረን፡፡
ጥበብን አግኝ፤ ማስተዋልን አግኝ፤ አትርሳም፥ ከአፌም ቃል ፈቀቅ አትበል። አትተዋት፥ ትደግፍህማለች፤ ውደዳት፥ ትጠብቅህማለች። ጥበብ ዓይነተኛ ነገር ናትና ጥበብን አግኝ፤ ከሀብትህም ሁሉ ማስተዋልን አትርፍ። ምሳሌ 4፡5-7
ጥበብ የሚገኘው ከእግዚአብሄር ነው፡፡ በእምነት ወደፈእግዚአብሄር በመፀለይ ጥበብን እንቀበላለን፡፡
ከእናንተ ግን ማንም ጥበብ ቢጎድለው፥ ሳይነቅፍ በልግስና ለሁሉ የሚሰጠውን እግዚአብሔርን ይለምን፥ ለእርሱም ይሰጠዋል። ያዕቆብ 1፡5
ሌላው ጥበብ የሚገኘው በእግዚአብሄር ቃል ውስጥ ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል መረዳት ጥበበኛ ያደርጋል፡፡
ከሕፃንነትህም ጀምረህ ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን፥ መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን ቅዱሳን መጻሕፍትን አውቀሃል። 2ኛ ጢሞቴዎስ 3፡15
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ጥበብ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ማስተዋል #እምነት #ፈተና #ፀሎት #ጌታ #የእግዚአብሄርቃል #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
The Beauty of Simplicity!
God created mankind simple. He created him and commanded him to eat everything except the tree of the knowledge of good and evil.
But man disobeyed God and did exactly what He told him not to do, since then life is complicated.
This only have I found: God created mankind upright, but they have gone in search of many schemes.” Ecclesiastes 7:29
Man lost his simplicity. He has fallen into complexity. It was not so from the beginning. When a person is developed he is developed into simplicity and not to not complexity. Simplicity is a real development. Simplicity is the ultimate sophistication.
The more you know God, the more you want your life to be simple.
Let’s see what the bible says about the blessings of simplicity and the danger of life complexity.
Jesus warns us from complication of trusting money that hinders the rich from going to heaven.
Indeed, it is easier for a camel to go through the eye of a needle than for someone who is rich to enter the kingdom of God. Luke 18:25
Command those who are rich in this present world not to be arrogant nor to put their hope in wealth, which is so uncertain, but to put their hope in God, who richly provides us with everything for our enjoyment. 1 Timothy 6:17
Speak in simplicity. Don’t complicate your speech. Keep your words short and to the point. Keep your words as few as you can manage.
All you need to say is simply ‘Yes’ or ‘No’; anything beyond this comes from the evil one. Matthew 5:37
Sin is not ended by multiplying words, but the prudent hold their tongues. Proverbs 10:19
Man is created for truth. We are wired for truth. So speak the truth. Don’t complicate your life in lies. That is the reason lie detector detects unnatural behavior.
Therefore each of you must put off falsehood and speak truthfully to your neighbor, for we are all members of one body. Ephesians 4:25
Don’t complicate you’re giving. Keep you’re giving simple. Give without expecting a repayment.
But when you give a banquet, invite the poor, the crippled, the lame, the blind, and you will be blessed. Although they cannot repay you, you will be repaid at the resurrection of the righteous. Luke 14:13, 14
Think simple. Don’t complicate your life by trying to do God’s part. Keep it simple in doing your only part of prayer and trust in his doing his part. Don’t complicate things trying to figure out or handle which you can’t. Focus on prayer and rest in God.
Cast all your anxiety on him because he cares for you. 1 Peter 5:7
Don’t complicate yourself by obeying when only seen and not obeying by nor seen.
Obey them not only to win their favor when their eye is on you, but as slaves of Christ, doing the will of God from your heart. Ephesians 6:6
Don’t complicate yourself fighting for luxury. Keep it simple in necessity.
What causes fights and quarrels among you? Don’t they come from your desires that battle within you? You desire but do not have, so you kill. You covet but you cannot get what you want, so you quarrel and fight. You do not have because you do not ask God. When you ask, you do not receive, because you ask with wrong motives, that you may spend what you get on your pleasures. James 4:1-3
Learn to be contented. Learn to live within your means.
But if we have food and clothing, we will be content with that. 1 Timothy 6:8
Don’t complicate your standard in life. Don’t favorite the rich don’t be a respecter of persons. Treat everyone with respect. Don’t have a double standard.
My brothers and sisters, believers in our glorious Lord Jesus Christ must not show favoritism. Have you not discriminated among yourselves and become judges with evil thoughts? James 2:1, 4
Resign from competition. Keep your potential to the calling of God. Don’t waste your energy on vain a competition.
The world is full of competition. But we are not of this world. We are called to specific purpose in life. We can’t compete with anyone.
We do not dare to classify or compare ourselves with some who commend themselves. When they measure themselves by themselves and compare themselves with themselves, they are not wise. 2 Corinthians 10:12
We are created for simplicity of love. Hatred is debt. Hatred is burden. Bitterness is abnormality.
Let no debt remain outstanding, except the continuing debt to love one another, for whoever loves others has fulfilled the law. Romans 13:8
Don’t relax too much.
Be alert and of sober mind. Your enemy the devil prowls around like a roaring lion looking for someone to devour. 1 Peter 5:8
Don’t be distracted by many things keep it simple. Don’t eat, drink and relax too much.
But you be watchful in all things, endure afflictions, do the work of an evangelist, fulfill your ministry. 2 Timothy 4:5 (NKJV)
but few things are needed–or indeed only one. Mary has chosen what is better, and it will not be taken away from her.” Luke 10:42
Keep your life simple from sin complex. Avoid being destructed from your calling to holiness by sin and lust.
Therefore, since we are surrounded by such a great cloud of witnesses, let us throw off everything that hinders and the sin that so easily entangles. And let us run with perseverance the race marked out for us, Hebrews 12:1
Keep your simplicity of sincerity.
But I am afraid that just as Eve was deceived by the serpent’s cunning, your minds may somehow be led astray from your sincere and pure devotion to Christ. 2 Corinthians 11:3
For More Articles https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#God #Jesus #simplicity #simple #knowledge #rejoice #trustgod #grace #salvation #church #testimony #rejoice #preaching #Bible #theword #Abiydinsa #scriptures #abiywakumadinsa
የወዳጅነት ጥበብ
በሰው ህይወት ውስጥ በጣም ከፍተኛ ስፍራ ካላቸው ነገሮች አንዱ ወዳጅነት ነው፡፡
ወዳጅነት የሌላውን ስሜት መረዳት ይጠይቃል፡፡ ወዳጅነት የሌላን ድንበር ማክበር ይጠይቃል፡፡ ወዳጅነት አንዱ ሌላውን ማገልገልን ይጠይቃል፡፡ ወዳጅነት አንዱ የአንዱን ሸክምን መሸከምን ይጠይቃል፡፡
ሰው የራሱ የግሌ የሚለው ክልል አለው፡፡ ሰው ለራሱ ብቻ የሚያስቀረው ሚስጥር ሊኖረው ይችላል፡፡ ሰው ለራሱ ብቻ የሚፈቅደው ግላዊነት ይኖረዋል፡፡ ያንን የግል ክልል ማክበር ወዳጅነትን ያጠናክራል፡፡
ወዳጅነት አንዱ ለሌላው መድረስን ያካትታል፡፡ መፅሃፍ ቅዱስ ወዳጅ በዘመኑ ሁሉ እንደሚወድ ያስተምረናል፡፡
ወዳጅ በዘመኑ ሁሉ ይወድዳል፤ ወንድምም ለመከራ ይወለዳል ምሳሌ 17፡17
ወዳጅነት ሃላፊነት ነው ፡፡ ወዳጅነት ማካፈል ነው፡፡ ወዳጅነት ለሌላው መገኘት ነው፡፡ ወዳጅነት መስጠት ነው፡፡ ሰው ለሁሉም ሊሰጥ አይችልም፡፡ ለሁሉም ሊሰጥ የሚፈልግ ሰው ለማንም ሳይሰጥ ይቀራል፡፡ ስለዚህ ነው መፅሃፍ ቅዱስ መርጠን በመልካም በወዳጅነት ላይ ኢንቨስት እንድናደርግ የሚያስተምረን፡፡
ብዙ ወዳጆች ያሉት ሰው ይጠፋል፤ ነገር ግን ከወንድም አብልጦ የሚጠጋጋ ወዳጅ አለ። ምሳሌ 18፥24
ወዳጅነት በአንድ ዘመን ብቻ የሚያበቃ አይደለም፡፡ ወዳጅነት ለትውልድ ይተላለፋል፡፡ አንዳንዴ ከዘመድ ይልቅ ወዳጅ ቀድሞ ይደርሳል ይጠቅማልም፡፡
ወዳጅህንና የአባትህን ወዳጅ አትተው፤ በመከራህም ቀን ወደ ወንድምህ ቤት አትግባ፤ የቀረበ ወዳጅ ከራቀ ወንድም ይሻላል። ምሳሌ 27፥10
ወዳጅነት በመተማመን ላይ ብቻ ይመሰረታል፡፡ ስለዚህ ነው ወዳጅነት በአንድ ለሊት የማይገነባው፡፡ አንዱ ለሌላው ያለውን መሰጠት በማየት ነው አንዱ ለሌላው ራሱን የሚሰጠው፡፡ ወዳጁ ያለውን ታማኝነት በማየት ነው በታማኝነት ራሱን ለወዳጅነቱ ቀስ በቀስ የሚሰጠው፡፡ ወዳጅነትን ሊያፈርስ የሚመጣውን ነገር በጥንቃቄ መከታተል ይጠይቃል፡፡
ጠማማ ሰው ጥልን ይዘራል፤ ጆሮ ጠቢ ሰው የተማመኑትን ወዳጆች ይለያያል። ምሳሌ 16፥28
ወዳጅ በመልካም መንገድ በወዳጁ ላይ ተፅእኖ ያሳድራል፡፡ ትጉህ ወዳጅ ወዳጁን ትጉህ ያደርገዋል፡፡ አስተዋይ ወዳጅ ወዳጁን ማስተዋል እንዲጨምር ይረዳዋል፡፡ እንደ ወዳጅ በወዳጁ ላይ ተፅእኖ ለማድርግ ሰፊ እድል ያለው የለም፡፡
ከጠቢባን ጋር የሚሄድ ጠቢብ ይሆናል፤ የሰነፎች ባልንጀራ ግን ክፉ መከራን ይቀበላል። ምሳሌ 13፡20
ብረት ብረትን ይስለዋል፥ ሰውም ባልንጀራውን ይስላል። ምሳሌ 27፡17
ጻድቅ ለባልንጀራው መንገዱን ያሳያል፤ የኀጥኣን መንገድ ግን ታስታቸዋለች። ምሳሌ 12፡26
ወዳጅ ያሳርፋል፡፡ ወዳጅ ያስደስታል፡፡
ሽቱና ዕጣን ልብን ደስ ያሰኛሉ፤ እንዲሁ ነፍስ በወዳጁ ምክር ደስ ይላታል። ምሳሌ 27፡9
በተቃራኒው ደግሞ ከክፉ ባልንጀርነት መሸሽ ህይወትን ይጠብቃል፡፡ በባልንጀርነት አመል እንዳይበላሽ መጠንቀቀ ያስፈልጋል፡፡
ከቍጡ ሰው ጋር ባልንጀራ አትሁን፥ ከወፈፍተኛም ጋር አትሂድ፥ መንገዱን እንዳትማር ለነፍስህም ወጥመድ እንዳታገኝህ። ምሳሌ 22፡24-25
አትሳቱ፤ ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ያጠፋል። 1ኛ ቆሮንቶስ 15፡33
ወዳጅነት ምህረት ይቅር ማለት መሸከም ይጠይቃል፡፡ ማንም ሰው የማንወድለት ይህን ቢያስተካክል የምንለው ነገር አለው፡፡ ሁሉም ነገሩ የሚያስደስተን ሰው በምድር ላይ የለም፡፡ ስለዚህ ሌላውን መሸከም የሰውን መልካምነት እንድንጠቀም ያስችለናል፡፡ ራስ ወዳድ የሆነ ሰው ግን መለየት ነው የሚፈልገው፡፡ ራስ ወዳድ የሆነ ሰው ወረተኛ ነው፡፡ ራስ ወዳድ የሆነ ሰው በወዳጅነት አይፀናም፡፡ ራስ ወዳድ የሆነ ሰው ከወዳጅነት በላይ ሌሎች ጥቅሞችን በማስቀደም ታላቁን ስጦታ ወዳጅነትን ይጥላል፡፡
መለየት የሚወድድ ምኞቱን ይከተላል፥ መልካሙንም ጥበብ ሁሉ ይቃወማል። ምሳሌ 18፡1
ወዳጅነትን የሚያከብር ሰው በምህረት ይመላለሳል፡፡ ለወዳጅነት ዋጋ የሚሰጥ ሰው ወዳጅነትን የሚያጠፋውን ነገር ላለማድረግ ይጠነቀቃል ዋጋም ይከፍላል፡፡
ኃጢአትን የሚከድን ሰው ፍቅርን ይሻል፤ ነገርን የሚደጋግም ግን የተማመኑትን ወዳጆቹን ይለያያል። ምሳሌ 17፡9
ወዳጅነት በመተማመን ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ወዳጅ ወዳጁን እጅግ በጣም ከማመኑ የተነሳ ከጠላት መሳም ይልቅ የወዳጅ ማቁሰል እንኳን ተቀባይነት አለው፡፡
የተገለጠ ዘለፋ ከተሰወረ ፍቅር ይሻላል። የወዳጅ ማቍሰል የታመነ ነው፤ የጠላት መሳም ግን የበዛ ነው። ምሳሌ 27፡5-6
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ወዳጅ #ጓደኛ #መታመን #ጥበብ #ፍቅር #ኢየሱስ #ክርስቶስ #ጌታ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #እምነት #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ምህረት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
ህይወት እንደ ሲና ቡና
(Life is Like a cup of coffee) ከሚለው የተተረጎመ
ከኮሌጅ የተመረቁና በስራቸውም ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሱ ባለሙያዎች የድሮ የዩኒቨርሲቲ መምህር ፕሮፌሰራቸውን ለመጎብኘት በአንድነት ተሰበሰቡ፡፡ ውይይቱ በፍጥነት በስራና በህይወት ውጥረት ላይ ወደ ማጉረምረም ተለወጠ፡፡
ፕሮፌሰሩ ለእንግዶቹ ቡና ለማቅረብ ወደ ኩሽና ሄዶ አንድ ትልቅ ጀበና ቡናና አንዳንዱ ልሙጥ ፣ አንዳንዱ ውድ ፣ አንዳንዱ የሚያምር ከሸክላ የተሰራ ሲኒ ፣ ከፕላስቲክ የተሰራ ሲኒ ፣ ከብርጭቆ የተሰራ ሲኒ ይዞላቸው መጣና ራሳቸውን አንዲያስተናግዱ ነገራቸው፡፡
ሁሉም ተማሪዎች አንድ አንድ ቡና ሲኒ እንደያዙ ፕሮፌሰሩ እንዲህ አለ: “አስተውላችሁ ከሆነ ርካሾቹና ልሙጦቹ ሲኒዎች ተትተው የሚያምሩትና ውዶቹ ሁሉም ሲኒዎች ተወስደዋል፡፡ ለራሳችሁ ምርጥ ነገር መፈለጋችሁ የሚጠበቅ ቢሆንም የህይወታችሁ ውጥረትና ችግር ምንጭ ይኸው ነው፡፡
ሲኒው ለቡናው ጥራት ምንም አስተዋፅኦ አያደርግም፡፡ አንዳንዴ እንዳውም ብዙ ብር ያስወጣል፡፡ አንዳንዴም የምንጠጣውን ቡና ይደብቀዋል፡፡ ሁላችሁም በእርግጥ የሚያስፈልጋችሁ ቡናው እንጂ ሲኒው አይደለም፡፡ ነገር ግን አስባችሁ ምርጡን ሲኒ አነሳችሁ፡፡ ከዚያም በኋላ አንዳችሁ የሌላችሁን ሲኒ ማየት ጀመራችሁ፡፡
ተመልከቱ ሕይወት ቡናው ነው፡፡ በኅብረተሰቡ ውስጥ ያለን ስራ ፣ ገንዘብ እና የህይወት ደረጃ አቋም ሲኒዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ሲኒዎች ሕይወትን የሚይዙ መያዣዎች እቃዎች እንጂ ህይወት አይደሉም፡፡ የምንጠጣበት ሲኒ ቡናውን ሊገልፀው አይችልም ወይም የምንኖረውን ህይወት ጥራት አይለውጠውም፡፡
አንዳንድ ጊዜ ሲኒው ላይ ብቻ በማተኮር በቡናው መደሰት ያቅተናል፡፡ ቡናውን አጣጥም እንጂ ሲኒውን አይደለም!
እጅግ ደስተኛ ሰዎች ሁሉ ምርጥ ነገር ሁሉ የላቸውም፡፡ ነገር ግን ካላቸው ነገር ምርጥ ነገርን ማውጣት ይችላሉ፡፡
በቀላሉ ኑር ፣ በልግስ ውደድ ፣ ለሌላው በሚገባ አስብ ፣ በደግነት ተናገር፡፡
ኑሮዬ ይበቃኛል ለሚለው ግን እግዚአብሔርን መምሰል እጅግ ማትረፊያ ነው፤ 1ኛ ጢሞቴዎስ 6፡6
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ራስንማማጠን #ደስተኝነት #ያለኝይበቃኛል #ህይወት #ዘላለም #ኢየሱስ #ክርስቶስ #ጌታ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #እምነት #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #መንገድ #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
የህይወት ጥያቄ መልስ
ጥበብ ትጣራለች
በአሜሪካ የሚገኙ ሁሉ ሊያነቡት የሚገባ
የሰይጣን ማታለያ መንገዶች
-
· ክፍፍልና ፉክክር
-
· ይቅር አለማለት
-
· የዚህም ዓለም አሳብና የባለጠግነት ማታለል
-
· ትዕቢት
የጻድቃን መንገድ
ሚስቶች ያሉአቸው እንደሌላቸው
ልባችሁን በመንገዳችሁ ላይ አድርጉ
የህይወት ሚዛን
ቃሉን መተግበር
ድንበር ይከበር!
-
ሰው የእግዚአብሄርን ፈቃድ ከተረዳና ካደረገው በኋላ የእግዚአብሄርን ድርሻ መተው አለበት፡፡ የተስፋ ቃሉን መስጠት የእግዚአብሄር ስራ ነው፡፡ ሰው የእግዚአብሄርን ፈቃድ ካደረገ በኋላ ማረፍ ዘና ማለት አለበት፡፡ እግዚአብሄር ብቻ የሚፈፅመውን የተስፋ ቃሉን በራሱ ሊፈፅም መታገል የለበትም፡፡
-
ሰው የእግዚአብሄርን ፅድቅና መንግስቱን ከፈለገ እግዚአብሄር ስለሚፈፅመው መብልና ልብስ መጨነቅ የለበትም፡፡ የእግዚአብሄርን ፅድቅና መንግስቱን መፈለግ ለክርስቲያን በቂ ሃላፊነት ነው፡፡ የእግዚአብሄርን መንግስትና ፅድቁን በመፈለግ ብቻ እርፍ ሊልና ደስ ሊሰኝ ይገባዋል፡፡
-
በህይወታችን ፅድቅን መራብና መጠማታችን በቂ ነው፡፡ የሚያጠግበው እግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡ ነገር ግን ተርበንም እራሳችንን ለማጥገብም ከሞከርን ድንበር እያለፍን ስለሆነ ተስፋ እንቆርጣለን፡፡
-
በመንፈሳዊ ህይወታችን ለማደግ ማድረግ የምንችለው ውስን ነገር ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ማጥናትና መታዘዝ ፣ ወደእግዚአብሄር መፀለይ ከቅዱሳን ጋር ህብረትን ማድረግ የእኛ ሃላፊነት ነው፡፡ ሰው ግን ይህንን ካደረገ በኋላ ራሱን ሊያሳድግ በሚሞክረው ሙከራ ይረበሻል፡፡ የሚያሳድግ እግዚአብሄር ብቻ ነውና፡፡
-
ሰው የዛሬን ሃላፊነቱን ከተወጣ ማረፍ ደስ መሰኘት የሰላም እንቅልፉን መተኛት አለበት፡፡ ሰው ግን የነገን ሃላፊነት ዛሬ ሊሰራው ሲሞክር ሰላሙን ያጣል፡፡ ህይወቱን ደስ ሊሰኝበት ያቅተዋል፡፡
-
ሰው ክፋትን ሲሰራብን መቆጣት የእኛ ሃላፊነት ነው፡፡ ነገር ግን በቀልና ብድራትን መመለስ የእኛ ሃላፊነት አይደለም፡፡ ተቆጥተንም ብድራትንም ለመመለስ ስንሞክር ካለአቅማችን የእግዚአብሄርን ድርሻ ለመስራት እየሞከርን ነውና አይሳካልንም፡፡ እግዚአብሄርንም አይደሰትብንም፡፡ ነገር ግን ድርሻችንን አውቀን ለቁጣው ስፍራ መስጠት አለብን፡፡
-
ለክርስቲያን በኑሮም ሆነ በቃል ወንጌልን መስበክ የእለት ተእለት ስራው ነው፡፡ ነገር ግን ሰውን መለወጥ የሰው ስራ አይደለም፡፡ የሰው የወንጌል አገልግሎቱ የሚለካው በሚኖረው የህይወት ምስክርነትና በቃል የሚመሰክረው ምስክርነት ትጋት ብቻ እንጂ ጌታን በተቀበሉስ ሰዎች ብዛት አይደለም፡፡ የሚወቅስ መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡
ቀዳሚው ጥሪ
ባሪያዎች ሆይ፥ ለክርስቶስ እንደምትታዘዙ በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ በልባችሁ ቅንነት በሥጋ ጌቶቻችሁ ለሆኑ ታዘዙ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ እንደሚያደርጉ እንደ ክርስቶስ ባሪያዎች እንጂ ለሰው ደስ እንደምታሰኙ ለታይታ የምትገዙ አትሁኑ። ለሰው ሳይሆን ለጌታ እንደምትገዙ በትጋትና በበጎ ፈቃድ ተገዙ፤ ባሪያ ቢሆን ወይም ጨዋ ሰው፥ እያንዳንዱ የሚያደርገውን መልካም ነገር ሁሉ ከጌታ በብድራት እንዲቀበለው ታውቃላችሁና። እናንተም ጌቶች ሆይ፥ ዛቻውን ትታችሁ እንዲሁ አድርጉላቸው፥ በእነርሱና በእናንተ ላይ የሚገዛው ጌታ በሰማይ እንዳለ ለሰው ፊትም እንዳያደላ ታውቃላችሁና። ኤፌሶን 6፡5-9
የስኬት ቁልፍ
በፈቃዱ ውስጥ እንዳለው በምን አውቃለው?
በዝምታ ያፈራል!
The Way to Glory
- You are not the only person When you understand that everyone is tempted it gives you the energy to bear it.
- There will never be too much price to pay compared to the glory coming
- God will always provide a way out also. We trust our father God to have the answer for the test. It is on Him.
- God’s faithfulness doesn’t allow Him to let us be tempted beyond what we can bear.
- The wisdom that comes from God works for us in this situation. One of the meanings of wisdom is to know what to do when we don’t know what to do.
- We are benefited from persevering in the test of life. It makes us matured lacking nothing. Because you know that the testing of your faith produces perseverance.
- Our response should be rejoicing as God is in control and things are actually working together for our good.
ስድስቱ የፆም በረከቶች
5 things Christian shouldn’t do during political tensions
በፖለቲካ ውጥረት ወቅት ክርስቲያን ማድረግ የሌለበት 5 ነገሮች
- ጥበብን አለመጣል
- ራስን ከጥላቻ መጠበቅ፡፡
- ሰለአገር መፀለይን አለመተው
- በፖለቲካ ከወንድም አለመለየት
- ክርስትናን ማስቀደም
The Power is in our hands!
ስልጣኑ በእጃችን ነው !
በህይወት ደስተኛ ለመሆን
ጊዜው አሁን ነው!
For the Foundations of the Earth are the Lord’s
የምድር መሠረቶች የእግዚአብሔር ናቸውና!
አትታበዩ፥ በኩራትም አትናገሩ፤ እግዚአብሔር አዋቂ ነውና፥ እግዚአብሔርም ሥራውን የሚመዝን ነውና፥ ከአፋችሁ የኵራት ነገር አይውጣ። የኃያላንን ቀስት ሰብሮአል፥ ደካሞችንም በኃይል ታጥቀዋል። ጠግበው የነበሩ እንጀራ አጡ፤ ተርበው የነበሩ ከራብ ዐርፈዋል፤ መካኒቱ ሰባት ወልዳለችና፥ ብዙም የወለደችው ደክማለች። እግዚአብሔር ይገድላል ያድናልም፤ ወደ ሲኦል ያወርዳል፥ ያወጣል። እግዚአብሔር ድሀ ያደርጋል፥ ባለጠጋም ያደርጋል፤ ያዋርዳል፥ ደግሞም ከፍ ከፍ ያደርጋል። ከሕዝቡ መኳንንት ጋር ያስቀምጣቸው ዘንድ፥ የክብርንም ዙፋን ያወርሳቸው ዘንድ፥ ችግረኛውን ከመሬት ያስነሣል፥ ምስኪኑንም ከጉድፍ ያስነሣል፤ የምድር መሠረቶች የእግዚአብሔር ናቸውና፥ በእነርሱ ላይም ዓለምን አደረገ። 1ኛ ሳሙኤል 2፡3-8
Boast in the Lord
ሃይል አያስመካም ማስተዋል እንጂ
ሁላችንም ሯጮች ነን
-
ውጤት ለሁሉም አይደለም፡፡ የክርስትናውን ሩጫ ከሌላ የሚለየውና ደግነቱ ከአንድ እስከ ሶስት የወጣ ብቻ የሚሸለምበት እንደ አካል ብልት ሁላችንም ለተለያየ ተግባር ስለተጠራን በዚህ ሩጫ በሚገባ የሮጠ ሁሉ ይሸለማል፡፡
-
ለመዳን እየሱስ በመስቀል ላይ በሰራው ስላ ማመን ብቻ ሲጠይቅ ለመሸለም ግን ውሳኔን ይጠይቃል፡፡ በክርስትና ህይወት የሚሸለመው በድንገት አይደለም፡፡ ለአክሊል በትጋት በውሳኔና በእውቀት የሰራ ይሸለማል፡፡ ለዚህ ነው መፅሃፍ ታገኙ ዘንድ ሩጡ የሚለው።
-
ሩጫ ትግስትንና ጥበብን ይጠይቃል፡፡ ሩጫ ሰውነትን መግዛትና ዲሲፒሊን ይጠይቃል፡፡ ውጤት ቁጥብነትን ስለሚጠይቅ ሯጭ የሚያደርጋቸውና የማያደርጋቸው ነገሮች አሉ፡፡ ሯጭ የሚበላውና የማይበላው አለ፡፡ ሯጭ በሩጫው ውጤት ለማምጣት ሰውነቱን በነገር ሁሉ ይገዛል፡፡
-
የህይወት ሩጫ ሽልማት ከማንኛውም የኦሎምፒክ ሽልማት ይበልጣል፡፡ የምድር ሽልማት የሚጠፋ ሽልማት ነው፡፡ ይህ ሽልማት ስንሞት አብሮን የሚሄድ ሽልማት አይደለም፡፡ ይህ ሽልማት የመሬት ስበት ይዞ የሚያስቀረው ከነፍስና ከመንፈሳችን ጋር አብሮን ወደሰማይ የሚሄድ አይደለም፡፡ የህይወት ሽልማት የዘላለም ነው፡፡
-
ይህ የዘላለም ሽልማት ሩጫ በትኩረትና በአላማ የሚሮጥ ነው፡፡ በዚህ ሩጫ ላይ ስናተኩር በፊታችን ከሩጫችን የሚያስተጓጉሉንን እንቅፋቶች እናልፋለን፡፡ መንፈሳዊ ህይወታችን በቃሉ ሙሉ ፍሬ እንዳያፈራ ትኩረታችንን ሊከፋፍል የሚመጣውን የዚህም ዓለም አሳብና የባለጠግነት መታለል እንቃወማለን፡፡
-
ሩጫ ትግስት ፡ ጥበብና እርጋታን ይጠይቃል፡፡ የህይወት ሩጫ ማራቶን እንመሆኑ መጠን ጉልበት አለኝ ተብሎ የሚበረርበት አይደለም፡፡ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ ዕብራውያን 12፡1
-
የሩጫ ወደር የሌለው ምሳሌያችን ኢየሱስ ነው፡፡ እርሱን ተመልክተን እንደሱ ከሮጥን የማናሸንፍበት ምክኒያት የለም፡፡ እየሱስ በፊቱ ስላለው ዘላለማዊ ደስታ ብዙ ነገሮችን ንቋል፡፡
ስማችሁ በሰማያት ስለ ተጻፈ
ነገር ግን መናፍስት ስለ ተገዙላችሁ በዚህ ደስ አይበላችሁ፥ ስማችሁ ግን በሰማያት ስለ ተጻፈ ደስ ይበላችሁ። ሉቃስ 10፡20
እግዚአብሄር ለሃጢያታችን መድሃኒት ባዘጋጀው በእየሱስ ክርስቶስ አዳኝነትና ጌትነት በማመናችን ስማችን በህይወት መዝገብ ላይ ተፅፎአል፡፡ ስማችን በህይወት መዝገብ ላይ ስለተፃፈ ስንሞት ወይም ነፍሳችን ከስጋችን ሲለይ ከእግዚአብሄር ጋር ለዘላለም እንኖራለን፡፡
ነገር ግን እግዚአብሄር ያዘጋጀውን የመዳኛ መንገድ እየሱስን የጣሉና ያልተቀበሉ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደተዘጋጀው ወደ እሳት ባህር ይጣላሉ፡፡ ምክኒያቱም በታረደው በግ ሕይወት መጽሐፍ ስሞቻቸው ያልተጻፉ ሁሉ ለአሳቹ ለአውሬው ይሰግዳሉ፡፡
ከዓለምም ፍጥረት ጀምሮ በታረደው በግ ሕይወት መጽሐፍ ስሞቻቸው ያልተጻፉ በምድር የሚኖሩ ሁሉ ይሰግዱለታል። ራእይ 13፡8
በሕይወትም መጽሐፍ ተጽፎ ያልተገኘው ማንኛውም በእሳት ባሕር ውስጥ ተጣለ። ራእይ 20፡15
በምድር ላይ ከምናደርገው ማንኛውም ግኝትና ስኬት በላይ የሚያስደስተው ስማችን በህይወት መዝገብ ላይ ማፃፉና ወደመንግስተ ሰማያት እንደምንገባ ማረጋገጣችን ነው፡፡
በምድር ላይ ካሉ ደስታዎች ሁሉ ይልቅ ዘላቂው ደስታ ከእግዚአብሄር ጋር ለዘላለም እንድንኖር እግዚአብሄር እኛን ልጅ አድርጎ መቀበሉ ነው፡፡
በምድር ላይ ከምናገኛቸው ደስታዎች ሁሉ የሚበልጠው ከዚህ ጊዜያዊ ስጋ ስንለይ ዘላለማችንን የምናሳልፈው ከእግዚአብሄ ጋር መሆኑን ማወቃችን ነው፡፡
ነገር ግን መናፍስት ስለ ተገዙላችሁ በዚህ ደስ አይበላችሁ፥ ስማችሁ ግን በሰማያት ስለ ተጻፈ ደስ ይበላችሁ። ሉቃስ 10፡20
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#መንግስተሰማያት #ዘላለም #ስም #የህይወትመዝገብ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
ከእግዚአብሄር የመቀበያ ጥበብ
ብዙዎቻችን እግዚአብሄር ፀሎታችንን እንደሚሰማ እናምናለን እንፀያለንም፡፡ እውነትም እግዚአብሄርም ፀሎትን የሚመልስ ህያው አምላክ ነው፡፡
ግን ስንቶቻችን ነን የፀሎት መልሳችንን እንዴት ከእግዚአብሄር እንደምንቀበል የምናውቅ? መፀለያችን ብቻ ሳይሆን እንዴት የፀሎታችንን መልስ ከእግዚአብሄር እንደምንቀበል ካላወቅን በስተቀር እግዚአብሄር ፀሎትን የማይመልስ ሁሉ ሊመስለን ይችላል፡፡
ወይም ደግሞ እግዚአብሄር እንደሚባርክ አምነን ለእግዚአብሄር ገንዘባችንን እንሰጣለን፡፡ ለእግዚአብሄር ገንዘባችንን በመስጠታችን ምንም እንደማይጎድልብን እናምናለን፡፡ እውነትም ነው ለእግዚአብሄር ሰጥቶ የጎደለበት ሰው የለም፡፡
ለእግዚአብሄር ገንዘባችንን ስንሰጥ እግዚአብሄር ገንዘብን ሊሰጠን ይችላል፡፡ ነገር ግን እኛ ለእግዚአብሄር ገንዘባችንን ስንሰጥ እግዚአብሄር የሚሰጠን ገንዘብ ብቻ አይደለም፡፡
በህይወታችን ከእግዚአብሄር የምንፈልገው ነገር ገንዘብ ብቻ አይደለም፡፡ ከእግዚአብሄር የምንፈልገው ብዙ አይነት ነገር አለ፡፡ ገንዘብ ውስን ስለሆነ ገንዘብ ሊመልሳቸው የማይችላቸው ብዙ ጥያቄዎች በህይወታችን አሉ፡፡
እግዚአብሄርም መሃሪ ስለሆና የህይወታችንን የጊዜውን ጥያቄ በሚገባ መመለስ ስለሚፈልግ ለእግዚአብሄር ገንዘባችንን ስንሰጥ የሚሰጠን ወይም መልሶ የሚባርከን በገንዘብ ብቻ አይደለም፡፡ ከገንዘብ በላይ እጅግ አስፈላጊና ውድ ነገሮች በህይወታችን አሉ፡፡
እግዚአብሄር ገንዘብን ይሰጣል ገንዘብ ብቻ አይደለም እግዚአብሄር ሰላምን ይሰጣል፡፡ እግዚአብሄር እርካታን ይሰጣል፡፡ እግዚአብሄር ሞገስን ይሰጣል፡፡ እግዚአብሄር እረፍትን ይሰጣል፡፡ የምንበላውን እህልና ውሃ እንኳን የሚባርከው እግዚአብሄር ነው፡፡ እግዚአብሄር በሽታን ከመካከላችን ያርቃል ፡፡ ዘጸአት 23፡25
እግዚአብሄር ሲባርክ አንድን ጥሩ ነገር እንድናደርግ በምሪት ይባርከናል፡፡ ትክክለኛውን ነገር እንድናደርግ እግዚአብሄር በልብ መነሳሳት ይባርከናል፡፡ የማይቻለውን ነገር እንድናደርግ ያልተለመደ ድፍረትን ይሰጠናል፡፡ እርሻን አርሰን እንድንበላ ጉልበትን የሚሰጠን እንኳን እግዚአብሄር ነው፡፡
በልብህም፦ ጉልበቴ የእጄም ብርታት ይህን ሀብት አመጣልኝ እንዳትል። ዘዳግም 8፡17
ነግደን እንድናተርፍ እግዚእብሄር ጥበብን ይሰጠናል፡፡ እግዚአብሄር እንዲከናወንልን በሮችን ይከፍትልናል፡፡ ካለንበት ሁኔታ ውስጥ እንድንወጣ ቃልን በጊዜው የሚሰጠው እግዚአብሄር ነው፡፡ እነዚህን ፈላጊና ተፈላጊ የሚያገናኘው እግዚአብሄር ነው፡፡
እኔም ተመለስሁ፥ ከፀሐይ በታችም ሩጫ ለፈጣኖች፥ ሰልፍም ለኃያላን፥ እንጀራም ለጠቢባን፥ ባለጠግነትም ለአስተዋዮች፥ ሞገስም ለአዋቂዎች እንዳልሆነ አየሁ፤ ጊዜና እድል ግን ሁሉን ይገናኛቸዋል። መክብብ 9፡11
እግዚአብሄርን በህይወታችን የማንፈልግበት ሁኔታ የለም፡፡ እግዚአብሄርንም የሚባርከን በሁሉም መንገዶች ነው፡፡ ዞሮ ዞሮ ብልፅግና ማለት ብዙ ገንዘብ ማግኘት ብቻ ሳይሆን የምንፈልገውን ነገር በምንፈልግበት ጊዜ ማግኘት ነው፡፡
እንግዲህ በእኛ እንደሚሠራው ኃይል መጠን ከምንለምነው ወይም ከምናስበው ሁሉ ይልቅ እጅግ አብልጦ ሊያደርግ ለሚቻለው፥ ኤፌሶን 3፡20
ከእግዚአብሄር መቀበላችን የተረጋገጠ ነውና ወደእግዚአብሄር መፀለያችንንና ለእግዚአብሄር መስጠታችንን እናብዛ፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
የሚያስፈልገው አንድ ነገር
በህይወት እግዚአብሄር እንዳለልን በልቡና በነፍሱ እንዳለ መኖር የከበረ ነገር ነው፡፡ እግዚአብሄር የሚፈልገው ይህ ነው ብለን በግምት በመኖር ህይወታችንን ከምናባክን እግዚአብሄር የሚፈልገውን አግኝተንና አድርገን ማለፍ ወደር የማይገኝለት መታደል ነው፡፡
እግዚአብሄር ምን እንደሚፈልግ እንድንገምትለትና እንድናደርገው አልጠየቀንም፡፡ እግዚአብሄር የሚፈልገውን ግልፅ አድርጓል፡፡ የሚያስፈልገው ብዙ ነገር አይደለም፡፡
ሰዎች እግዚአብሄርን ለማስደሰትና ለማስደነቅ በራሳቸው የሚሄዱት ብዙ መንገዶች እግዚአብሄርን አያስደንቁትም፡፡ ሰዎች የሚያስፈልገውን ነገር ሳያደርጉ በአገልግሎት ስም ጭምር እግዚአብሄርን ለማስደሰት የሚያደርጉት ነገሮች እግዚአብሄር ጎሽ አይላቸውም፡፡
እግዚአብሄር የሚፈልገውን ያውቃል የሚፈልገውም እንዲደረግለት ይፈልጋል ይጠብቃል፡፡
እየሱስ እነማርያም ቤት ሲሄድ አላማው ቤተሰቡ የእግዚአብሄርን ቃል እንዲሰሙና ፈቃዱን እንዲረዱ ነው፡፡ ማርታ ግን በቤት ስራ ልታገለግለው ጉድ ጉድ በማለትዋ እየሱስ ወደቤተሰቡ የሄደበትን አላማ ፈፅሞ ሳተችው፡፡ እየሱስና ማርታ ተላለፉ፡፡
በዚያ ሰአት የማርታ ከምንም አስቀድሞ የእግዚአብሄርን ቃል መስማት ወደር የማይገኝለት የህይወት ምርጫ ነበር፡፡ እርስዋ ግን እየሱስ ይፈልጋል ብላ ያሰበችውን እንጂ እየሱስ የፈለገውን አላደረገችም፡፡
እርስዋ ለእየሱስ መልካም ነው ብላ የገመተችውን በማድረግ ልታገለግለው ደፋ ቀና ትል ነበር፡፡ ያ እየሱስን አላስደሰተውም፡፡ ብዙ ነገር በማድረጉዋ እያገለገለች እያስደሰተችው መሰላት፡፡
እግዚአብሄር በህይወታችን ቅድሚያ እንድንሰጠው የሚፈልገው ነገር ቃሉን መስማት ነው፡፡ ከኑሮ ከስራ ከአገልግሎትም ከሩጫም በፊት ቅድሚያ ሊሰጠው የሚያስፈልገው ቃሉን መስማት ነው፡፡
እንዲያውም እየሱስ የሚያስፈልገው ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው አለ፡፡ የሚያስፈልገው በአለም ሩጫና ባተሌነት ሳይወሰዱ ረጋ ብሎ እግዚአብሄር ከኔ ምን ይፈልጋል ብሎ የእግዚአብሄርን ፈቃድ ለማግኘት ጊዜን መስጠትና ያንን ማድረግ ነው፡፡
ሲሄዱም እርሱ ወደ አንዲት መንደር ገባ፤ ማርታ የተባለች አንዲት ሴትም በቤትዋ ተቀበለችው። ለእርስዋም ማርያም የምትባል እኅት ነበረቻት፥ እርስዋም ደግሞ ቃሉን ልትሰማ በኢየሱስ እግር አጠገብ ተቀምጣ ነበረች። ማርታ ግን አገልግሎት ስለ በዛባት ባከነች፤ ቀርባም፦ ጌታ ሆይ፥ እኔ እንድሠራ እኅቴ ብቻዬን ስትተወኝ አይገድህምን? እንኪያስ እንድታግዘኝ ንገራት አለችው። ኢየሱስም መልሶ፦ ማርታ፥ ማርታ፥ በብዙ ነገር ትጨነቂአለሽ ትታወኪማለሽ፥ የሚያስፈልገው ግን ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው፤ ማርያምም መልካም ዕድልን መርጣለች ከእርስዋም አይወሰድባትም አላት። ሉቃስ 10፡38-42
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ
ሕይወታችሁ ምንድር ነው?
በአለም ላይ ያለው ነገር ሁሉ አላፊ ጠፊም ነው፡፡ የሚታየው ነገር ሁሉ ያልፋል፡፡ ሁሉም ነገር ያልፋል፡፡ ምክኒያቱም የሚታየው ነገር ሁሉ ከማይታየው ነው የመጣው፡፡
ዓለሞች በእግዚአብሔር ቃል እንደ ተዘጋጁ፥ ስለዚህም የሚታየው ነገር ከሚታዩት እንዳልሆነ በእምነት እናስተውላለን። ዕብራውያን 11፡3
አሁን በአይን የሚታየው ነገር ሁሉ ሃላፊ ነው ፡፡ መንፈሳዊው አለም በአይን የማይታየው አለም ብቻ ነው ቋሚና የማያልፈው፡፡
የሚታየው የጊዜው ነውና፥ የማይታየው ግን የዘላለም ነው። 2ኛ ቆሮንቶስ 4፡18
የሰውን ህይወት እንኳን ስንመለከት ከዘላለም ጋር ሲነፃፀር ህይወቱ ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፍዋለት ነው፡፡
ሕይወታችሁ ምንድር ነው? ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፍዋለት ናችሁና። ያዕቆብ 4፡14
ስለዚህ ነው መፅሃፍ ቅዱስ በላይ ያለውን እሹ የሚለው፡፡ በላይ ያለው መንፈሳዊው አለም ዘላቂውና ቋሚው አለም ብቻ ነው አስተማማኝ ፡፡ እርሱ ብቻ ነው የማያልፈው፡፡
እንግዲህ ከክርስቶስ ጋር ከተነሣችሁ፥ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ ባለበት በላይ እሹ፤ በላይ ያለውን አስቡ እንጂ በምድር ያለውን አይደለም። ቆላስይስ 3፡1-2
ለዘላለም የሚኖረው ሰማዩንና ምድሩን የፈጠረው የእግዚአብሄር ቃል ነው፡፡ እንዲሁም የእግዚአብሄርን ቃል የሚያደርግ ሰው ለዘላለም ይኖራል፡፡
ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል። 1ኛ ዮሐንስ 2፡17
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
#ኢየሱስ #ጌታ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #እንፍዋለት #ሕይወታችሁ #ዘላለም #የእግዚአብሄርቃል #የእግዚአብሔርፈቃድ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
ከፊታችን ያሉ መልካም ቀኖች
እንደ ንጽሕት ድንግል
በእግዚአብሔር ቅንዓት እቀናላችኋለሁና፥ እንደ ንጽሕት ድንግል እናንተን ለክርስቶስ ላቀርብ ለአንድ ወንድ አጭቻችኋለሁና፤ ነገር ግን እባብ በተንኮሉ ሔዋንን እንዳሳታት፥ አሳባችሁ ተበላሽቶ ለክርስቶስ ከሚሆን ቅንነትና ንጽሕና ምናልባት እንዳይለወጥ ብዬ እፈራለሁ። 2ኛ ቆሮንቶስ 11፡2-3
ሃሳብ በጣም ጥንቃቄ የሚፈልግ ነገር ነው፡፡ ሃሳብ ይነፃል ሃሳብ ይበላሻል፡፡ ሃሳብ ሲበላሽ ቅንነትና ንፅህና ይለወጣል፡፡ ቅን እና ንፁህ የነበረው ሰው ጠማማ እና የተጣመመ ሃሳብ ያለው ሰው ይሆናል፡፡
ሰው ሃሳቡ ሲበላሽና ቅንነቱ ሲለወጥ በእግዚአብሄር ማመኑን ያቆማል፡፡ ይህ በእግዚአብሄር ላይ ያለው እምነቱ መቀነሱ የሚታወቀው በአፉ ተናግሮት አይደለም፡፡ እግዚአብሄርን ማመን የከበደው ሰው በድርጊቱ ይታወቃል፡፡
ሰው ቅንነቱ ሲለወጥ ለመንፈሳዊ መሪዎች ያለው አክብሮት ይቀንሳል፡፡ ሰው ሃሳቡ ሲበላሽ ለቤተክርስቲያን ያለው መሰጠት ይቀንሳል፡፡ ለቤተክርስቲያን ገንዘቡን ሰጥቶ የማይጠግበው ሰው ቅንነቱ ሲበላሽ መጠራጠር ይጀምራል፡፡ ሰው ቅንነቱ ሲበላሽ የእግዚአብሄርን ህዝብ ማገልገል መፍራት ይጀምራል፡፡ የእግዚአብሄርን ህዝብ በትጋት በማገልገል የሚታወቀው ሰው ሃሳቡ ሲበላሽ ጊዜውንና ጉልበቱን መሰሰት ይጀምራል፡፡ ሰው ቅንነቱ ሲበላሽ ከእግዚአብሄር ህዝብ ጋር ህብረት ላለማድረግ ሰንካላ ምክኒያቶች ይበቁታል፡፡ ሰው ቅንነቱ ሲበላሽ ለሰዎች ስለጌታ ከሃጢያት አዳኝነት መናገር ይቀንሳል፡፡ ሰው ቅንነቱ ሲበላሽ ከፀሎት ይልቅ ሌሎች ነገሮች ያምሩታል፡፡
ጌታ እንዲነግዱና እንዲያተርፉ ንጉስ መክሊትን ስለሰጣቸው ምሳሌ ሲናገር አንድ መክሊት የተሰጠው ለንጉሱ ያለው ሃሳብ ስለተበላሸና ቅንነቱ ስለተለወጠ መክሊቱን ወስዶ ቀበረው፡፡
አንድ የተቀበለው ግን ሄዶ ምድርን ቈፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ። አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፦ ጌታ ሆይ፥ ካልዘራህባት የምታጭድ ካልበተንህባትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ፈራሁም ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ እነሆ፥ መክሊትህ አለህ አለ። ማቴዎስ 25፡18, 24-25
እንዲነግድ እንዲያተርፍና እንዲያድግ እንዲሾም የተሰጠውን መክሊት የቀበረው ምክኒያቱ የንጉሱን አላማ ስለተጠራጠረና ለንጉሱ ያለው ሃሳብ ሰለተበላሸ በዚያም ቅንነቱ ስለተለወጠ ነው፡፡
እግዚአብሄርን ማገልገል ታላቅ ጥቅም እና ታላቅ እድል ነው፡፡ ራሳችሁን ተመልከቱ ተመለሱም፡፡ ሃሳባችሁ እንዳይበላሽና ቅንነታችሁ እንዳይለወጥ ትጉ፡፡ ሃሳባችሁ እንዲለወጥ የሚመጣውን ማንኛውንም ሃሳብ አትቀበሉ፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ብቻ እመኑ፡፡
በእግዚአብሔር ቅንዓት እቀናላችኋለሁና፥ እንደ ንጽሕት ድንግል እናንተን ለክርስቶስ ላቀርብ ለአንድ ወንድ አጭቻችኋለሁና፤ ነገር ግን እባብ በተንኮሉ ሔዋንን እንዳሳታት፥ አሳባችሁ ተበላሽቶ ለክርስቶስ ከሚሆን ቅንነትና ንጽሕና ምናልባት እንዳይለወጥ ብዬ እፈራለሁ። 2ኛ ቆሮንቶስ 11፡2-3
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
#አተረፈ #ንፅህና #ቅንነት #ንጉስ #መክሊት #ኢየሱስ #ጌታ #መፅሃፍቅዱስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ስብከት #እምነት
ተቃወሙ!
የዲያቢሎስ አላማ አንድና አንድ ነው፡፡ ዲያቢሎስ ከመጣ ሊሰርቅ ሊያርድ ሊያጠፋ ነው፡፡ ከዚህ ውጪ ለሌላ ነገር አይመጣም፡፡
ዲያቢሎስንብ የመጋዣው መንገድ ደግሞ በእግዚአብሄር ላይ ማመፅ ወደ እግዚአብሄር አለመጠጋትና ከሃጢያት ጋር መጫወት ነው፡፡
ዋነኛው ታዲያ ዲያቢሎስን የመቃወሚያው መንገድ ለእግዚአብሄር መገዛት ነው፡፡ ዲያቢሎስን የመቃወም ውጤታማው መንገድ ወደ እግዚአብሄር መቅረብ ነው፡፡
እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል፤ ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ ወደ እናንተም ይቀርባል። እናንተ ኃጢአተኞች፥ እጆቻችሁን አንጹ፤ ሁለት አሳብም ያላችሁ እናንተ፥ ልባችሁን አጥሩ። ያዕቆብ 4፡7-8
ልጆች ሆነን ሸንኮራ ስንመጥ የምንጥለው ምጣጭ ዝንብን ይስባል፡፡ ዝንብን መከላከያው ውጤታማው መንገድ የዝንብ ማባረሪያና መግደያ አይደለም፡፡ ምክኒያቱም ዝንብን የሚስበው ቆሻሻ ስለሆነ ቆሻሻው እስካለ ድረስ ሁሌ ዝንብ ይሳባል፡፡ ዝንብ ቆሻሻን ማሳደድ ተፈጥሮው ስለሆነ ቆሻሻን አስቀምጠን ዝንብ አይምጣ ማለት አንችልም፡፡
ነገር ግን ዝንብን የማባረሪያው መንገድ አካባቢን ማፅዳት ነው፡፡ አካባቢውን ከፀዳ ዝንብ ቢመጣ እንኳን የሚፈልገውን ስለማያገኝና እዚያ አካባቢ መቆየት ስራ መፍታትና ጊዜ ማባከን ስለሚሆንበት ዝንብ አይቆይም፡፡
እንዲሁ ሰይጣንን በህይወታችን እንዳይሰርቅ እንዳያርድና እንዳያጠፋ የምናደርግበት ዋነኛው መንገድ ሀጥያትን መፀየፍ ከክፉ የወጣትነት ምኞት መሸሽ ነው፡፡
ሰው ፍምን በብብቱ ታቅፎ አያቃጥለኝ ማለት እንደማይችል ሁሉ ሃጢያትን እየሰራ ሰይጣን አይስረቀኝ ማለት አይችልም፡፡ ሰው ለሰይጣን ተስማሚ ለም መሬት የሆነውን ጥላቻን በልቡ ይዞ ሰይጣን በህይወቴ አያጥፋ አይግደል የማለት አቅሙ አይኖረውም፡፡
ለሰይጣን ፍቱምን መድሃኒቱ እርሱን የሚስቡትን ነገሮች ሃጢያትንና ጥላቻን ከህይወት ማራቅ ነው፡፡ ሰይጣንን የመቃወሚያው መንገድ ለእግዚአብሄር እንደቃሉ መገዛትና ወደ እግዚአብሄር መቅረብ ነው፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ
ሳታቋርጡ ፀልዩ
ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፤ ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና። 1ኛ ተሰሎንቄ 5፡16-18
በህይወት ማሸነፍ እንዴት ደስ የሚል ነገር ነው፡፡ ሰው በህይወቱ ሁል ጊዜ ካለማቋረጥ ማሸነፍ ይችላል፡፡
እኛ የእግዚአብሄር የክብሩ መገለጫ እቃዎች ነን፡፡ በራሳችን ምንም ማድረግ አንችልም፡፡ እግዚአብሄር ላይ በታመንን መጠን ሁሉ ግን ሁሌ እናሸንፋለን የሚሳነንም ነገር አይኖርም፡፡
ሳታቋርጡ ድል እንድታደርጉ ሳታቋርጡ ጸልዩ፡፡
መፀለይና ማሸነፍ ይቻላል፡፡ ነገር ግን ሁሌ ማሸነፍ ይቻላል? አንዳንድ ሰዎች ይህ ሊደረስበት የማይቻል ነገር እንደሆነ ያስቡታል፡፡
መልሱ ግን አዎን ሳያቋርጡ በመፀለይ ሁሌ ማሸነፍ ይቻላል ነው፡፡ ማረጋገጫው ምንድነው ብሎ ለሚጠይቅ ሰው ሁሉ መልሱ እግዚአብሄር የማይቻል ነገር አያዝዝም ፡፡ እግዚአብሄር ካዘዘ ይቻላል ማለት ነው ፡፡
ሳያቋርጡ መፀለይ ማለት ሁሌ ተንበርክኮ መፀለይ ማለት ግን አይደለም፡፡ መፀለይ መንበርከክን ወይም በርን መዝጋትን ቢያጠቃልልም በእነዚህ ብቻ አይወሰንም፡፡
ሳያቋርጡ መፀለይ ማለት ካለማቋረጥ በእግዚአብሄር ላይ መደገፍ ፣ ካለማቋረጥ ልብን ለእርዳታ ወደ እግዚአብሄር ማንሳት እና ሌላም ስራ እየሰሩም ቢሆን ካለማቋረጥ በውስጥ ከእግዚአብሄር ጋር መነጋገር ማለት ነው፡፡ ፀሎት በውስጥ ለእርዳታ ወደ እግዚአብሄር መጮኽ ነው፡፡
እግዚአብሄር የልብን ጩኸት ይሰማል፡፡
እግዚአብሄር አንዳንዴ ብቻ ሳይሆን ሁሌ እንዲሳካልን ስለሚፈልግ ሳታቋርጡ ጸልዩ እያለ እየጋበዘን ነው፡፡
ሳናቋርጥ በመፀለይ ሳናቋርጥ እንከናወን፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
#ኢየሱስ #ጌታ #ፀሎት #የእግዚአብሄርእርዳታ #የልብጩኸት #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #አማርኛ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
በምድር ተቀመጥ
በምድር ስንኖር የእግዚአብሄርን ፈቃድ በምድር እንዳንፈፅም ሊያስፈሩን የሚመጡ ብዙ ነገሮች አሉ፡፡
አንዳንድ ሰው ወጥቶ ህይወትን መጋፈጥ ሲፈራ ተኝቶ መዋል ያምረዋል፡፡ ሌላው ደግሞ ቶሎ ወደ ሰማይ እንዲሄድ ይመኛል፡፡ የሆነ ቦታ ብቻ መሄድ ከምድር መውጣት ይፈልጋል፡፡
በጌታ በእየሱስ ያመነ ሰው ወደሰማይ የሚሄድበት ጊዜ አለው፡፡ ላሁን ግን የሚሰራ ስራ ስላለ በዚሁ በምድር ይቆያል፡፡
አንዳንዴ የሰዎችን ክፋት ስናይ ዘመኑ ያስፈራራናል፡፡ የፍርሃቱን ስሜት ከሰማነው ሽምድምድ አድርጎ ሊያስቀምጠን ነው የሚመጣው፡፡
የኑሮውን ውድነት ስታስብ እንዴት ነው የሚኖረው ትል ይሆናል፡፡ የእግዚአብሄር አምላካዊ መልስ ግን ይህ ሁሉ ችግሮች ባሉባት በዚችሁ ምድር ተቀመጥ ታምነህ ተሰማራ ነው፡፡
እግዚአብሄር ግን የሚፈልገው በዚህ በእንግድነት አገራችን በምድር ላይ ታምነን እንድኖር ነው፡፡
እዚሁ ጠላት ባለበት ምድር ላይ ኖረህ እንድታሸነፍ ነው እንጂ ጌታ ከአለም እንድትወጣ አይደለም የሚፈልገው፡፡
እግዚአብሄርን ከማመናችን በፊት ምድር እየተሻሻለች መሄድ የለባትም፡፡ ከማሸነፋችን በፊት የሰዎች ባህሪ መሻሻል የለበት፡፡ እንዲሳካልን ሰዎች ሁሉ በእግዚአበሄር ማመን የለባቸውም፡፡
አለም ግን ወዴት እየሄደች ነው ብለን በሞራል መላሸቅ መገረማችንን እያለ እንዲያውም እየበዛ እግዚአብሄር እንዲህ ይላል፡፡
በእግዚአብሔር ታመን፥ . . . በምድርም ተቀመጥ፥ ታምነህም ተሰማራ ነው የሚለው፡፡
- እዚሁ ጨለማ ምድርን ድቅድቅ ጨለማ አህዛብን በሚሸፍንበት ነው ብርሃንህን ሊያወጣ የሚፈልገው፡፡
ብርሃን መቷልና የእግዚአብሄርም ክብር መቷልና ተነሽ አብሪ። እነሆ ጨለማ ምድርን ድቅድቅ ጨለማ አህዛብን ይሸፍናሉ ነገር ግን በአንች ላይ እግዚአብሄር ይወጣል ክብሩም በአንች ላይ ይታያል፡፡ መዝሙር 60፡1-2
- በሞት ጥላ መካከል ነው አብሮህ መሆን የሚፈልገው፡፡
በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኵዝህ እነርሱ ያጸናኑኛል። መዝሙር 23፡4
- በጠላቶችህ ፊት ለፊት ነው ራስህን በዘይት መቀባት የሚፈልገው፡፡
በፊቴ ገበታን አዘጋጀህልኝ፤ በጠላቶቼ ፊት ለፊት ራሴን በዘይት ቀባህ፥ ጽዋዬም የተረፈ ነው። መዝሙር 23፡5
- እዚሁ ደረቁ ምድር ላይ መቶ እጥፍ እንድታፈራ የሚፈልገው፡፡
ይስሐቅም በዚያች ምድር ዘርን ዘራ፥ በዚያች ዓመትም መቶ እጥፍ አገኘ እግዚአብሔርም ባረከው። ዘፍጥረት 26፡12
እግዚአብሄር ግን ታምነን እንድኖር ነው የሚፈልገው፡፡ ለዚህ ነው በምድር ተቀመጥ ታምነህ ተሰማራ የሚለው፡፡
በእግዚአብሔር ታመን፥ መልካምንም አድርግ፥ በምድርም ተቀመጥ፥ ታምነህም ተሰማራ። መዝሙር 37፡3
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች
#ድፍረት #መተማመን #እምነት #መፅሃፍቅዱስ #አማርኛ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
ብፁሃን የዋሆች
የዋሆች ብፁዓን ናቸው፥ ምድርን ይወርሳሉና። ማቴዎስ 5፡5
የዋህ በአማርኛ መዝገበ ቃላት ” ገር ፣ ቅን ፣ መሠሪነት የክፋት ብልጠት የሌለው ” በማለት ተተርጉሟል፡፡
የዋህ ማለት በሰው ላይ ክፉ ለማድረግና ለግሉ አላግባብ ለመጠቀም አቅሙና ችሎታው እያለው ሰውን ላለመጉዳት የሚጠነቀቅ ሃይሉን ለክፋት የማይጠቀምና ከክፋት የሚከለከል ሰው ማለት ነው፡፡
የዋህነት ደካማነት አይደለም፡፡ የዋህነት እንዲያውም ብርታት ነው ፡፡ ጀግና የሚባለው ራሱን የማይገዛ ሰው ሳይሆን ክፋት ለማድረግ ሲፈተን ራሱን የሚገዛ ለክፋት እጅ የማይሰጥ ብርቱ ሰው ነው፡፡
የዋህነት ሞኝነት አይደለም፡፡ እንዲያውም የዋህነት ሁኔታውን ጥበበኛው እግዚአብሄር እንዲይዘው ለጌታ የመተው ብልጠት ነው፡፡ የዋህነት ራስ የመበቀልን ፈተና በማለፍ ብድራቱን ለሚመልሰው ለእግዚአብሄር እድሉን መስጠት ነው፡፡
ተወዳጆች ሆይ፥ ራሳችሁ አትበቀሉ፥ ለቍጣው ፈንታ ስጡ እንጂ፤ በቀል የእኔ ነው፥ እኔ ብድራቱን እመልሳለሁ ይላል ጌታ ተብሎ ተጽፎአልና። ሮሜ 12:19
የዋህነት የሰው ቁጣ የእግዚአብሔርን ፅድቅን እንደማይሰራ በመረዳት ለእግዚአብሄር ገዢነት እውቅና መስጠት ነው፡፡ የሰው ቍጣ የእግዚአብሔርን ጽድቅ አይሠራምና። ያዕቆብ 1፡20
የዋህነት “ብትበደሉ አይሻልምን?” የሚለውን የእግዚአብሄርን ቃል አምኖ ሌላውን ከመበደል ይልቅ ራስ በመበደል ከእግዚአብሄር ሽልማት መቀበል ነው፡፡
እንግዲህ ፈጽሞ የእርስ በርስ ሙግት እንዳለባችሁ በእናንተ ጉድለት ነው። ብትበደሉ አይሻልምን? ብትታለሉስ አይሻልምን? 1ኛ ቆሮንቶስ 6፡7
የዋህነት ለእግዚአብሄር አምላክነት እውቅና መስጠት ነው፡፡ የዋህነት እግዚአብሄርን ምንጭ ማድረግ ነው፡፡ የዋህነት አላግባብ ከሰው አለመጠበቅ ነው፡፡ የዋህነት የስኬት ቁልፍ ያለው በምድር እንዳይደለ ማወቅ ነው፡፡ የዋህነት በጥበብ በሃይል በባለጠግነት አለመመካት ነው፡፡ ይልቁንም የዋህነት ፅድቅና ፍርድን ምህረትን የሚያደርግ እግዚአብሄር መሆኑን በማወቅ መመካት ነው፡፡
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ጠቢብ በጥበቡ አይመካ፥ ኃያልም በኃይሉ አይመካ፥ ባለ ጠጋም በብልጥግናው አይመካ ነገር ግን የሚመካው። ምሕረትንና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ የማደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን በማወቁና በማስተዋሉ በዚህ ይመካ ደስ የሚያሰኙኝ እነዚህ ናቸውና፥ ይላል እግዚአብሔር፦ ኤርምያስ 9፡23-24
የዋህነት እግዚአብሄርን ያስደስተዋል፡፡ በየዋህነት እግዚአብሄርን ካስደሰትነው ምድርን እንወርሳለን፡፡ የዋሆች ብፁዓን ናቸው፥ ምድርን ይወርሳሉና። ማቴዎስ 5፡5
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ተስፋ #ፍቅር #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ
ዘመኑን ግዙ
እንግዲህ እንደ ጥበበኞች እንጂ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንዴት እንድትመላለሱ በጥንቃቄ ተጠበቁ፤ ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ። ኤፌሶን ሰዎች 5፡15-16
ብዙ ሰዎች የሚሳሳቱትና ከስኬት የሚወድቁት ቀኖቹ ለእነርሱ እንደሚሰራላቸው ባለማስተዋል በማሰብ ነው፡፡ ሰዎች ዘመኑ መልካም እንደሆነ ነገር ዘና ሲሉና በማስተዋል ካልነቁ እግዚአብሄር ወዳየላቸው የክብር ደረጃ መድረስ ያቅታቸዋል፡፡
ቀኖቹ ክፉዎች ናቸው፡፡ በጥንቃቄ ሳንኖር ቀኖቹ በራሳቸው ዝም ብለው ለእኛ ይሰራሉ ብለን ከጠበቅን አንሳሳታለን፡፡ ቀኖቹ በራሳቸው ለእኛ በጎነት አይሰሩም፡፡ መልካሙ የምስራች ግን እነዚህን ክፉ ቀኖች ለእኛ እንዲሰሩ ማድረግ መቻላችን ነው፡፡ እነዚህን ክፉ ቀኖች መግዛት የሚቻልበትና ለእኛ ስኬት እንዲሰሩ የሚደረግበት መላ አለ፡፡
ክፉ ቀኖች ለእኛ እንዲሰሩ ብሎም እግዚአብሄር ወዳየልን የህይወት አላማ መድረስ የምንችለው በጥበብ ጥንቃቄ ስንመላለስ ነው፡፡
የእግዚአብሄር ቃል በሚሰጠን ጥበብ ከተመላለስን እነዚህን ክፉ ቀኖች ገልብጠን ለእኛ በጎነት እንዲሰሩ ማድረግ እንችላለን፡፡ በሚበልጥ በእግዚአብሄር ጥበብ ከኖርን ክፋታቸው በእኛ ላይ እንዳይሰራ አድርገን ከሁኔታዎች ሁሉ በላይ መኖር እንችላለን፡፡
ከሕፃንነትህም ጀምረህ ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን፥ መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን ቅዱሳን መጻሕፍትን አውቀሃል። 2ኛ ጢሞቴዎስ 3፡15
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢነት #ጥበብ #አቢይዋቁማ
ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ
ታላቅ ነው !
ልጆች ሆይ፥ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ አሸንፋችኋቸውማል፥ በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና። 1ኛ ዮሐንስ 4:4
በክርስትና ህይወታችን የትም አትሄድም ፣ በላሁህ ፣ ጣልኩህ ፣ አሁንስ አታመልጥም ብለው የሚያስፈራሩ ብዙ ነገሮች ይነሳሉ፡፡
በአካባቢያችን ያሉትን ሁኔታዎች በማሳየት እግዚአብሄር የተናገረን ነገር እንደማይሆንና ሊፈፀም እንደማይችል ሊያስረዱንና ሊያሳምኑን ይጥራሉ፡፡
ክርስትናን በሚገባ ለመኖር አቅም እንደሌለን የአለም ሃይል እንደሚያሸንፈን በብዙ ሊያሳምኑን የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም፡፡
ነገር ግን . . .
እግዚአብሄር በህይወታችን ያስቀመጠውን አላማ ሊቋቋም የሚችል ምንም ሃይል አልነበረም የለም ወደፊትም አይኖርም፡፡
እየሱስ በምድር ሲኖር አሸንፎ የእግዚአብሄርን ፈቃድ በሙላት እንደፈፀመ እኛንም ሊያሸንፈን የሚችል በፊታችን የሚቆም ምንም ሃይል የለም፡፡
በምድር ያለው ተግዳሮት እንደማናሸንፍ ማረጋገጫ ሊሆን በፍፁም አይችልም፡፡ እንዲያውም የተግዳሮት መኖር ወደአሸናፊነት እየገሰገስን እንደሆንንና ልናሸንፍ እንደምንችል ማረጋገጫው ነው፡፡
ከእኛ የተነሳ ሳይሆን በውስጣችን ካለው የተነሳ እንደምናሸንፍ ሳይታለም የተፈታ ነገር ነው፡፡
በእኛ ያለው በአለም ካለው ማንኛውም ተግዳሮትና ሃይል ሁሉ ይልቅ ታላቅ ነው፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር ቢያደርጉ
የአእምሮ ገዳም
የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ። ሮሜ 12፡2
ሰዎች እግዚአብሄርን በመፈለጋቸውና ከዚህ አለም ነፃ ለመውጣት በመፈለጋቸው ከአለም መሸሽና ገዳም መግባት ይፈልጋሉ፡፡ ይህንንም ለማድረግ ገዳም ቢገቡም ጠልተውት የመጡት ክፉ የሃጢያት ሃሳብ ተከትሎዋቸው ይመጣል፡፡ በዚህም ምክኒያት ምንም ከከተማ ወጥተው ገዳም ቢገቡም የአለማዊነት አስተሳሰብ በአእምሮአቸው እስካለ ድረስ ከአለም መለየት ያቅታቸዋል፡፡
መፅሃፍ ቅዱስ አለምን ስለማንመስልበት ገዳም ይናገራል፡፡ ይህን አለም አለመምሰል የምንችለው ብቸኛው መንገድ አእምሮዋችን በእግዚአብሄር ቃል ሲታደስና የአለም ክፉ አስተሳሰብ በልባችን ቦታ ሳያገኝ ሲቀር ብቻ ነው ፡፡
አለማዊ የሚያደርገን ከተማ መኖራችን ወይም ከሰው ተለይተን አለመኖራችን ሳይሆን አእምሮዋችን በእግዚአብሄር ቃል አለመታደሱና ከሃጢያት ሃሳብ ጋር መኖራችን ነው፡፡ አእምሮዋችን በእግዚአብሄር ቃል ሲቃኝና ሲለወጥ በህይወታችን ለአለማዊነት ምንም ስፍራ አይኖርም፡፡
አለማዊ ከሚያደርገን ከሃጢያት ሃሳብ ጋር እስካለን ድረስ ከከተማ ወጥተን ከሰው ተለይተን ገዳምም ብንገባ ከሃጢያት ባርነት አናመልጥም፡፡ ምክኒያቱም አለማዊ ከሚያደርገን የሃጢያት ክፉ ሃሳብ አእምሮዋችን እስካልታደሰ ድረስ አለምን አለመምሰል አንችልም፡፡
ነገር ግን ባለንበት በስራችን በምንኖርበት ቦታ ሁሉ በእግዚአብሄር ቃል አእምሮአችንን ካደስነው ይህን አለም ሳንመስል እግዚአብሄርን እያስደሰትን መኖርና ማገልገል እንችላለን፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ያድርጉ!
በላይ ያለውን እሹ
እንደ ሌባ
እየሱስ የሰው ልጆች ሰለ ደህንታቸው ምን እንዳደረጉ ሊጠይቅና በምድር ላይ ሊፈርድ ተመልሶ የሚመጣው እንደሌባ ድንገት ነው፡፡ ሰዎች የእለት ተእለት ኑሯቸውን እየኖሩ እየበሉ እየጠጡ እያገቡና እየተጋቡ ማንም ሳያውቅ ኢየሱስ በድንገት ይመጣል፡፡
ወንድሞች ሆይ፥ ስለ ዘመናትና ስለ ወራት ምንም እንዲጻፍላችሁ አያስፈልጋችሁም፤ የጌታ ቀን፥ ሌባ በሌሊት እንደሚመጣ፥ እንዲሁ ይመጣ ዘንድ ራሳችሁ አጥብቃችሁ አውቃችኋልና። 1ኛ ተሰሎንቄ 5፡1-2
እየሱስ በቶሎ እንደሚመጣ እንጂ በምን ቀንና ሰአት እንደሚመጣ አናውቅም፡፡ ማድረግ የምንችለው የተሻለ ነገር ተዘጋጅቶ መጠበቅ ብቻ ነው፡፡
የእግዚአብሄር ሰው ማርቲን ሉተር ክርስቶስ ትናንትና እንደሞተ ፡ ዛሬ ጠዋት እንደተነሳ ፡ ነገ ተመልሶ እንደሚመጣ አድርጋችሁ በዝግጅት ኑሩ በማለት ይመክራሉ፡፡
ስለዚያች ቀንና ስለዚያች ሰዓት ግን ከአባት ብቻ በቀር የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ ልጅም ቢሆን የሚያውቅ የለም። የኖኅ ዘመን እንደ ነበረ የሰው ልጅ መምጣት እንዲሁ ይሆናልና። በዚያች ወራት ከጥፋት ውኃ በፊት፥ ኖኅ ወደ መርከብ እስከገባበት ቀን ድረስ፥ ሲበሉና ሲጠጡ ሲያገቡና ሲጋቡም እንደ ነበሩ፥ የጥፋት ውኃም መጥቶ ሁሉን እስከ ወሰደ ድረስ እንዳላወቁ፥ የሰው ልጅ መምጣት ደግሞ እንዲሁ ይሆናል። ማቴዎስ 24፡36-39
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ያድርጉ!
እየሱስ ይመጣል
የሰው ልጆች ሁሉ በሃጢያት ሃይል ስር ወድቀው ነበር፡፡ ሰዎች ሁሉ በሃጢያት ምክኒያት ለዘላለም ከእግዚአብሄር በተለያዩ ጊዜ የሃጢያታቸውን እዳ ለመክፈል በመስቀል ላይ ለመሞት እየሱስ ወደ ምድር ላይ መጥቶ ነበር፡፡
እየሱስ የሞትን ሃይል አሸንፎ ከሞት ተነስቶአል፡፡ በክብርም አርጎ በእግዚአብሄር ቀኝ ተቀምጦዋል፡፡
አሁን ዓመተ ምህረት ወይም የምህረት አመት ነው፡፡ ማንም ሰው ሃጢያተኝነቱን ተረድቶ ሀጢያቱ ለዘላለም ከእግዚአብሄር እንደሚለየው አውቆ ንስሃ ለመግባት መልካመ አጋጣሚ ነው፡፡ የሰው ልጆች ንስሃ እንዲገቡና እንዲመለሱ በመታገስ እየሱስ በሰማይ ቆይቶዋል፡፡
እየሱስ ዋጋ የከፈለው ዘርና ሃይማኖት ሳይለይ ለሰው ልጆች ሁሉ ነው፡፡ እግዚአብሄር የሰውን ፊት አይቶ አያዳላም፡፡
ሰዎች ሁሉ ሊድኑና እውነቱን ወደ ማወቅ ሊደርሱ በሚወድ በእግዚአብሔር በመድኃኒታችን ፊት መልካምና ደስ የሚያሰኝ ይህ ነው። 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፡4
እየሱስ በቅርብ ተመልሶ ይመጣል፡፡
እነሆ፥ በቶሎ እመጣለሁ፥ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ። ራእይ 22፡12
የሚገርመው ነገር ግን ተመልሶ የሚመጣው የሃጢያት እዳ ሊከፍል የሰው ልጆችን ሊያድን በድካም አይደለም፡፡ በቅርቡ ተመልሶ ሲመጣ በሃይልና በስልጣን ለእያንዳንዱም እንደ ስራው ሊከፍል በመላዕክት ታጅቦ ነው የሚመጣው፡፡
በቶሎ እመጣለሁ የሚለው ቃል እየሱስን ለሚከተል ሰው የሚያስፈነድቅ የምስራች ሲሆን እየሱስን ላልተቀበለ የሚያርበደብድ አስፈሪ መልዕክት ነው፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ያድርጉ!
ማኅፀን ገብቶ ይወለድ?
የአይን መከፈት
ሰነፍ በልቡ
ሰነፍ በልቡ። አምላክ የለም ይላል። በሥራቸው ረከሱ፥ ጐስቈሉ በጎ ነገርን የሚሠራ የለም። መዝሙር 14፡1
ሰነፍ ወይም ሞኝ እግዚአብሄር የለም የሚለው በቃሉ አይደለም ፡፡ በቃሉ አውጥቶ ሲናገር ላይሰማ ይችላል፡፡ ነገር ግን ድርጊቱ ጮክ ብሎ እግዚአብሄር የለም ይላል፡፡
ሰው በልቡ እግዚአብሄር የለም ማለቱን ስንፍናውን የሚያሳዩ ድርጊቶች አሉ፡፡
ሰው እግዚአብሄን መፈለግ ትቶ የእርሱ የህይወት ቁልፍ በምድር ላይ እንዳለ የሚያስብ ከሆነ በአኳሃኑ እግዚአብሄር የለም እያለ ነው፡፡ እግዚአብሄርን ፈጥሮት እርሱን የማይፈልግና የሚገባውን ክብር የማይሰጥ ሰው ሞኝና ሰነፍ ሰው ነው፡፡ እግዚአብሄር እንደሌለ አድርጎ ለእግዚአብሄር ትኩረት የማይሰጥ ሰው ሞኝ ነው፡፡ በህይወቱ ለእግዚአብሄር ስፍራ የሌለው ሰው የማያስተውል ሰው ነው፡፡
ሰው ብልጠቱና አስተዋይነቱ የሚታወቀው የፈጠረውን እግዚአብሄርን ሲፈልግ ነው፡፡ የፈጠረውን እግዚአብሄርን ቸል ከማለት በላይ ሞኝነትና ስንፍና የለም፡፡
ሰነፍ በልቡ። አምላክ የለም ይላል። ረከሱ በበደላቸውም ጐሰቈሉ በጎ ነገርን የሚያደርጋት የለም። የሚያስተውል እግዚአብሔርንም የሚፈልግ እንዳለ ያይ ዘንድ እግዚአብሔር ከሰማይ የሰው ልጆችን ተመለከተ። መዝሙር 53፡1-2
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ያድርጉ!
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
እምነት ይመጣል
ምን ይጠቅማል ?
ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል? ወይስ ሰው ስለ ነፍሱ ቤዛ ምን ይሰጣል? ማቴዎስ 16:26
ሰው አለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ማለት በአለም ላይ ያለው ሀብት ሁሉ የእርሱ ቢሆን ፡ በአለም አንደኛ ዝነኛ ቢሆን ፡ በአለም ላይ የሚፈልገውን ነገር ሁሉ ለማድረግ የሚችል ሃያል ሰው ቢሆን ማለት ነው፡፡ ሰው አለሙን ሁሉ ቢያተፍ ነፍሱን ግን ቢያጎድል ምን ይጠቅመዋል?
መልሱ ምንም አይጠቅመውም፡፡
ከነፍስ ዋጋ ጋር ሲተያዩ እነዚህ ነገሮች ከንቱ የከንቱም ከንቱ ናቸው፡፡ እነዚህ ነገሮች ሁሉ ተደምረውና ከአንድ ነፍስ ጋር በፍፁም አይወዳደሩም፡፡
ሰው እነዚህን ሃብት ፡ ዝናና ፡ ሃይል ሁሉ ደምሮ ለነፍሱ ቤዛና ዋጋ ሊከፍልላት የማይበቁ እጅግ በጣም ጥቂት ነገሮች ናቸው፡፡
በምድር ላይ እነዚህን ነገሮች ብናጣ በአለም ላይ ማንም ባያውቀን ፡ የመጨረሻ ደካማ ሰዎች ብንሆን ፡ ከምንበላውና ከምንለብሰው ውጭ ምንም የሌለን ብንሆን እንኳን ነፍሳችንን ካላጣን አንጎድልም አንከስርም፡፡ ነፍሳችንን ላለማጉደል እነዚህን ነገሮች ሁሉ እንኳን ብንተው ተጠቃሚ ነን አትራፊም ነን፡፡
ነፍሳችንን ላለማጉደል የምንወስደው ማንኛውም እርምጃ ሁሉ ትክክለኛ የጠቢብ ውሳኔ ነው፡፡
ስለዚህ ነው ከመርፈዱ በፊት ጌታ እየሱስን ለመከተል መወሰን ያለብን፡፡
በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አለ፦ እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር፥ ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ። ነፍሱን ሊያድን የሚወድ ሁሉ ያጠፋታል፤ ስለ እኔ ግን ነፍሱን የሚያጠፋ ሁሉ ያገኛታል። 26 ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል? ወይስ ሰው ስለ ነፍሱ ቤዛ ምን ይሰጣል? ማቴዎስ 16: 24-26
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ያድርጉ!
የንጉስ ብልጫ
የትኛው ጥበብ ?
የህይወት ጥያቄ
ኢየሱስን ተመልክተን
ይቻላል – እግዚአብሄርን ማስደሰት
-
በዚህ ምድር ስንኖር በምድራዊ በአይናችን ከሚታየው ነገር ባሻገር የእግዚአብሄርን መንግስት ስናይና እግዚአብሄርን በውሳኔያችን ስናስቀድም ለእርሱ እውቅና ስንሰጥ እግዚአብሄርን ያስደስተዋል፡፡ ሮሜ 8፡14 እና ምሳሌ 3፡5-6
-
በዙሪያችን ከከበበን ነገሮች በላይ የእግዚአብሄርን ቃል ስናምን እግዚአብሄር ደስ ይለዋል፡፡ ሮሜ 4:18
-
በምድር ኑሮዋችን በአይን የማይታየውን የሰማያዊውን መንግስት ያውም መንግስተ ሰማያት በመጠበቅ ስንኖር እግዚአብሄርን እናስደስተዋለን፡፡ ፊሊጲስዩስ 3፡20
-
በእለት ኑሮዋችን በተፈጥሮ አይን የማይታየውን በውስጣችን የሚኖረውን ጌታ እየሰማንና እየታዘዝን ስንኖር እግዚአብሄር ይደሰታል፡፡ ገላቲያ 2፡20
-
በእምነት በሰማይ ቤት እንዳለን የምድር ኑሮዋችን ጊዜያዊ መተላለፊያ ብቻ እንደሆነ አድርገን እንደ እንግዳና መፃተኛ ስንኖር እግዚአብሄር ደስ ይለዋል፡፡ 1ኛ ጴጥሮስ 2፡11 እና 2ኛ ቆሮንጦስ 5፡7-8
-
በስጋዊ አይናችን የማይታየውን እግዚአብሄርን በኑሮዋችን ሁሉ እየፈራን ስንኖር እግዚአብሄር ደስ ይለዋል፡፡ ማቴዎስ 10፡28
ቤተ እግዚአብሄር
የክህደት ጥሪ
እንተያይ
ለፍቅርና ለመልካምም ሥራ እንድንነቃቃ እርስ በርሳችን እንተያይ፤ በአንዳንዶችም ዘንድ ልማድ እንደ ሆነው፥ መሰብሰባችንን አንተው እርስ በርሳችን እንመካከር እንጂ፤ ይልቁንም ቀኑ ሲቀርብ እያያችሁ አብልጣችሁ ይህን አድርጉ። ዕብራውያን 10፡24-25
ሁላችንም በፍቅር መኖር እንፈልጋለን፡፡ ከእኛ ይበልጥ በፍቅር የሚኖር ሰው ስናይ እንደእርሱ ለመሆን እንቀናለን፡፡ ፍቅር ለሰነፎች አይደለም፡፡ ፍቅር ትጋትን ይጠይቃል፡፡ ፍቅር ርካሽ አይደለም፡፡ ፍቅር በትጋትና በንቃት ሊጠበቅ ፡ ሊነቃቃና ሊታደስ ይገባዋል፡፡
ከሰል በደንብ እንዲቀጣጠልና በመቀጣጠል እንዲቆይ መራገብ እንደሚያስፈልገው ሁሉ ፍቅርም እንዲበረታና እንዲቆይና መነቃቃት ይገባዋል፡፡ ፍቅርን የሚያነቃቃው ደግሞ በትጋት መገናኘትና መተያየት ነው፡፡
መልካም ስራም እንዲሁ ትጋትንና ፅናትን ይጠይቃል፡፡ መልካም ስራ ጉልበትን ይጠይቃል፡፡ መልካም ስራ ፅናትንና ብርታትን ይጠይቃል፡፡ መልካም ስራ በትጋት ካልተቀጣጠለ እየሟሸሸ ይሄዳል ቀስ በቀስም ይጠፋል፡፡
በትጋት እርስ በእርስ መተያየት መልካምን ስራ ያነቃቃዋል፡፡ አንዳችን በአንዳችን እምነት እንበረታታለን ፡፡ እንዳችን እንዳችንን እንቀርፃለን፡፡ አንዳችን አንዳችንን እንሞርዳለን እንስላለን፡፡ በመሰብሰብና በመተያየት እንታደሳለን፡፡
ለፍቅርና ለመልካም ስራ እንድንነቃቃ የእግዚአብሄርን ቃል ከሚያምኑ ፡ ከሚኖሩትና ከሚናገሩ ሰዎች ጋር በትጋት እንሰብሰብ ፡፡ እንዴት ለጌታ እንደሚገባ እንደምንኖር እርስ በእርሳችን እንመካከር፡፡
አንዳንዴ መልካም የሰራን እየመሰለን እንስታለን፡፡ ሰው ከተሰበሰብንና እርስ በእርሳችን ከተያየን ሌላው ችግራችንን ይነግረናል፡፡ የሌላውንም ችግር አይተን ለጌታ እንዲኖር በፍቅር ማበረታታት ቤተሰባዊ ሃላፊነታችን ነው፡፡ አንዳችን የሌላው ጠባቂዎች ነን፡፡ ይህንንም የመሰብሰብ መልካም ልማድ አብልጠን እንድናደርግ መፅሃፍ ይመክረናል፡፡
ልጅነቴ
ክብርህን ሳይ እጠግባለሁ
እግዚአብሄርን ማምለክ ከሰማይ በታች እጅግ ልዩ ልምምድ ነው፡፡ እግዚአብሄርን ማየት እጅግ ያስደስታል፡፡ በእግዚአብሄር ክብርና መልካምነት መዋጥ መረስረስ መወሰድ የመጨረሻው ልምምድ ነው፡፡ ይህ ልምምድ በምድር ላይ ካሉ የሚያስደስቱ ልምምዶች እጅግ ይለያል፡፡ እግዚአብሄርን ማምለክ ከምንም ጋር የሚወዳደር አይደለም፡፡
ጌታን እየሱስን የሚወዱ ክርስቲያኖች ያለውና የነበረው የሚመጣውም ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ። አልፋና ዖሜጋ አንተ ነህ፡፡ አንተንና አንተን ብቻ እናመልካለን ይሉታል፡፡ ራእይ 1፡8
ስለዚህ ነው መዝሙረኛው ወደ እግዚአብሄር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ የሚለው እግዚአብሄርን በክብሩ ማየት ስለወደደ ነው፡፡ መዝሙር 122፡1
በእግዚአብሄር መገኘት የዘላለም ደስታና ፍስሃ አለ፡፡ እግዚአብሄርን ማምለክ ያድሳል ያለመልማል፡፡
የሕይወትን መንገድ አሳየኸኝ፤ ከፊትህ ጋር ደስታን አጠገብኸኝ፥ በቀኝህም የዘላለም ፍሥሐ አለ። መዝሙር 16፡11
እኔ ግን በጽድቅ ፊትህን አያለሁ፤ ክብርህን ሳይ እጠግባለሁ። መዝሙር 16፡15
እግዚአብሄርን ስናለምልክ የራሳችንን ድካም እንረሳለን፡፡ እግዚአብሄርን ስናመልክ በእግዚአብሄር ሃይል እንታደሳለን፡፡ እግዚአብሄርን ስናመለክ በጨለማ ውስጥ ብርሃንን እናያለን፡፡ እግዚአብሄርን ስናመለክ በእግዚአብሄር መልካምነት እንወሰዳለን እንማካለን እንረሰርሳለን፡፡
እግዚአብሄርን በውበቱ ስናየው ማስተዋሉ በማይመረመር በእግዚአብሄር እውቀት እርፍ እንላለን፡፡ እግዚአብሄርን ስናመልክ ተስፋችን ይለመልማል፡፡ እግዚአብሄርን ስናመልክ ራሳችንንና የከበቡንን ነገሮች እንረሳለን፡፡
ዓይኖችህ ንጉሥን በውበቱ ያዩታል፤ እነርሱም በሩቅ ያለች ምድርን ያዩአታል። ኢሳይያስ 33፡17
አምላካችሁንም እግዚአብሔርን ታመልኩታላችሁ፥ እርሱም እህልህንና ውኃህን ይባርካል፤ በሽታንም ከመካከልህ አርቃለሁ። ዘጸአት 23፡25
አምላኬ፥ አምላኬ፥ ወደ አንተ እገሠግሣለሁ፤ ነፍሴ አንተን ተጠማች፥ ሥጋዬ አንተን እንዴት ናፈቀች እንጨትና ውኃ በሌለበት በምድረ በዳ። ኃይልህንና ክብርህን አይ ዘንድ እንዲሁ በመቅደስ ውስጥ ተመለከትሁህ። መዝሙር 63፡1-2
ተጓደዱ
በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ እግዚአብሔርን የሚፈልግ ልብ ደስ ይበለው። እግዚአብሔርን ፈልጉት፥ ትጸናላችሁም ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ። 1ኛ ዜና 16፡10-11
እግዚአብሄር መልካም አምላክ ነው፡፡ እግዚአብሄር ይፈለጋል፡፡ ሰው እግዚአብሄርን ካልፈለገ ማንን ሊፈልግ ነው? እግዚአብሄር የሚፈለግ አምላክ ነው፡፡
ከሰማይ በታች ልናደርገው የሚገባ ከምንም ነገር እጅግ የሚሻልና የሚበልጥ ነገር እግዚአብሄርን መፈለግ ነው፡፡ ጊዜያችንን ጉልበታችንን ሁለንተናችንን ልናፈስበት የሚገባው እጅግ አትራፊ ነገር እግዚአብሄርን ሁልጊዜ መፈለግ ነው፡፡
በመፅሃፍ ቅዱስም እንድጓደድ ወይም እንድንመካ የተፈቀደልን አንድ ነገር እግዚአብሄርን መፈለጋችን ነው፡፡
ከሰማይ በታች ምንም የሚያስመካ ነገር የለም፡፡ እንዲያውም ሰዎች በሚመኩበት ነገር እንዳንመካ እግዚአብሄር አስጠንቅቆዋል፡፡
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ጠቢብ በጥበቡ አይመካ፥ ኃያልም በኃይሉ አይመካ፥ ባለ ጠጋም በብልጥግናው አይመካ ኤርምያስ 9፡23
ነገር ግን የተፈቀደ ልንመካበት የምንችልበትና መመካት የሚገባን አንድ ነገር እግዚአብሄርን መፈለጋችን ነው፡፡ እግዚአብሄርን መፈለግ ባለጠግነትና ስኬት ነው፡፡ እግዚአብሄርን መፈለግ ሰላምና እርካታ ነው እግዚአብሄርን መፈለግ ደስታና ሙላት ነው፡፡ እግዚአብሄርን እንደመፈለግ የሚያፀናና የሚያስመካ ነገር የለም፡፡
ባለጠጎች ደኸዩ፥ ተራቡም፥ እግዚአብሔርን የሚፈልጉት ግን ከመልካም ነገር ሁሉ አይጐድሉም። መዝሙር 34፡10
ነገር ግን የሚመካው። ምሕረትንና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ የማደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን በማወቁና በማስተዋሉ በዚህ ይመካ ደስ የሚያሰኙኝ እነዚህ ናቸውና፥ ይላል እግዚአብሔር፦ ኤርምያስ 9፡24
እግዚአብሄርን መፈለግ ያስመካል፡፡ በሌላ በምንም ነገር አትመካ ነገር ግን እግዚአብሄርን በመፈለግህ ተጓደድ ደስ ይበልህ ተመካ፡፡
በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ እግዚአብሔርን የሚፈልግ ልብ ደስ ይበለው። እግዚአብሔርን ፈልጉት፥ ትጸናላችሁም ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ። 1ኛ ዜና 16፡10-11
አሕዛብ ይፈልጋሉ
እግዚአብሄር የአላማ አምላክ ነው፡፡ እግዚአብሄር ሰውን ከመፍጠሩ በፊት እንደዚህ ሰውን እንፍጠር ብሎ እንዳቀደና እንደፈጠረ ሁሉ እኛም ሳንወለድ በፊት የተወለድንበት አላማ ነበረ፡፡ እንጂ በምድር ላይ የተወለድነው በአጋጣሚ አይደለም፡፡ ወይም ደግሞ ከተወለድን በኋላ አይደለም የህይወት አላማ የተፈለገልን ፡፡ ከመወለዳችን በፊት የነበረን አላማ ለመፈፀም ተወልደናል፡፡
በምድር ላይ ሰርተን ለመፈፀምና ለእግዚአብሄር ክብር የምናመጣለት ከመወለዳችን በፊት የነበረ የመኖራችን ልዩ ምክኒያት ነበረ፡፡
እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ፤ ዮሃንስ 17፡4
ስለዚህ በማለዳ ከአልጋችን የሚያስነሳን እግዚአብሄርን የማክበር አላማን የመፈፀም ረሃብ እንጂ የምግብ ረሃብ አይደለም፡፡ ከአልጋችን የሚቀሰቅሰን ሰዎችን የማገልገል ጥማት እንጂ ለራስ መኖር አይደለም፡፡ ከአልጋችን የሚያስነሳን እግዚአብሄርን በምድር ለማክበር ያለብን መቃጠል እንጂ የሚበላና የሚጠጣ ፍላጎት አይደለም፡፡
እንግዲህ። ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤ ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ማቴዎስ 6፡31-32
በምድር ላይ የሚኖር ማንኛውም ሰው ሁሉ የሚበላውንና የሚጠጣውን ይፈልገዋል፡፡ አህዛብ በምድር ላይ ዋነኛ አላማቸው መብላት መጠጣት እንደ ማንኛውም ሰው ኖሮ ኖሮ መሞት ነው፡፡ እንዲያውም አህዛብ ከሚበላና ከሚጠጣ በስተቀር እግዚአብሄርን የማክበር ምንም አላማ የላቸውም፡፡
እየሱስ አህዛብ የሚኖሩለት የህይወት አላማ የእናንተም የኑሮ አላማ መሆን የለበትም እያለ ነው፡፡ እግዚአብሄርን ከማክበር የህይወት አላማችን ጋር ሲተያይ ይህ ለእኛ ተራ ነገር ነው፡፡ ይህ ለእግዚአብሄር ልጆች አይመጥንም፡፡ ይህ ለእግዚአብሄር ክብር ለሚኖሩ ሰዎች አይገባም፡፡ ይህ ለእግዚአብሄር ለሚኖሩ ሰዎች ከመለኪያ ደረጃ በታች የሆነ የህይወት ደረጃ ነው፡፡
ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል። ማቴዎስ 6፡32-32
ጣሉት
ታመን
በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፡፡ ምሳሌ 3፡5
ህይወት የእግዚአብሄር ውድ ስጦታ ነው፡፡ ይህን ስጦታ በሚገባ መያዝና መጠቀም ማስተዋል ይጠይቃል፡፡ የህይወትን ስጦታ በሚገባ ለመጠቀም ወደ ሰጭው መመለስና ለምን እንደሰጠንና ምን እንድናደርግበት እንደሰጠን መረዳት ይጠይቃል፡፡
በሌላ አነጋገር በምድር ላይ ለእግዚአብሄር ክብር ለመኖር ሁልጊዜ በእግዚአብሄር ምሪት ላይ መደገፍ ይጠበቅብናል፡፡
የእግዚአብሄርን ስጦታ ህይወትን በራስህ ማስተዋል አትኖረውም፡፡ የእግዚአብሄርን የህይወት ስጦታ በእግዚአብሄር እውቀትና ምሪት መጠቀም ይጠይቃል፡፡
ሁል ጊዜ በራሳችን እውቀትና ማስተዋል ነገሮችን ለማድረግ እንፈተናለን፡፡ ነገር ግን የራሳችን ማስተዋል ያስተናል እንጂ የትም አያደርሰንም፡፡
አሳቤ እንደ አሳባችሁ መንገዳችሁም እንደ መንገዴ አይደለምና ይላል እግዚአብሔር፦ ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል፥ እንዲሁ መንገዴ ከመንገዳችሁ አሳቤም ከአሳባችሁ ከፍ ያለ ነው። ኢሳያስ 55፡8-9
በእግዚአብሄር የምትታመነውና የምትደገፈው ለእግዚአብሄር አዋቂነትና ፍፁም መሪነትና እውቅና በመስጠት ነው፡፡ ይህን በማለት ለእግዚአብሄር እውቅና ልንሰጥ ይገባናል፡፡
- እኔ ከመፈጠሬ በፊት ለእኔ ያቀድከው ሃሳብ አለ
- የእኔ የህይወት እቅድና ንድፍ በአንተ ዘንድ አለ
- እኔ ለራሴ ከማውቀው በላይ አንተ ለእኔ ታውቃለህ
- አንተ ለእኔ ያለህ አላማ የፍቅር አላማ ነው
- አንተ ለእኔ የምታስበው ሃሳብ መልካም ብቻ ነው
በማለት ይህንን እግዚአብሄር ለህይወታችን ያለውን ሃሳብ ከእግዚአብሄር መፈለግና መከተል መንገዳችን እንዲቃና ያደርጋል፡፡
ምሳሌ 3፡6 በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ፥ እርሱም ጎዳናህን ያቀናልሃል።
ታመን
በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፡፡ ምሳሌ 3፡5
ህይወት የእግዚአብሄር ውድ ስጦታ ነው፡፡ ይህን ስጦታ በሚገባ መያዝና መጠቀም ማስተዋል ይጠይቃል፡፡ የህይወትን ስጦታ በሚገባ ለመጠቀም ወደ ሰጭው መመለስና ለምን እንደሰጠንና ምን እንድናደርግበት እንደሰጠን መረዳት ይጠይቃል፡፡
በሌላ አነጋገር በምድር ላይ ለእግዚአብሄር ክብር ለመኖር ሁልጊዜ በእግዚአብሄር ምሪት ላይ መደገፍ ይጠበቅብናል፡፡
የእግዚአብሄርን ስጦታ ህይወትን በራስህ ማስተዋል አትኖረውም፡፡ የእግዚአብሄርን የህይወት ስጦታ በእግዚአብሄር እውቀትና ምሪት መጠቀም ይጠይቃል፡፡
ሁል ጊዜ በራሳችን እውቀትና ማስተዋል ነገሮችን ለማድረግ እንፈተናለን፡፡ ነገር ግን የራሳችን ማስተዋል ያስተናል እንጂ የትም አያደርሰንም፡፡
አሳቤ እንደ አሳባችሁ መንገዳችሁም እንደ መንገዴ አይደለምና ይላል እግዚአብሔር፦ ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል፥ እንዲሁ መንገዴ ከመንገዳችሁ አሳቤም ከአሳባችሁ ከፍ ያለ ነው። ኢሳያስ 55፡8-9
በእግዚአብሄር የምትታመነውና የምትደገፈው ለእግዚአብሄር አዋቂነትና ፍፁም መሪነትና እውቅና በመስጠት ነው፡፡ ይህን በማለት ለእግዚአብሄር እውቅና ልንሰጥ ይገባናል፡፡
- እኔ ከመፈጠሬ በፊት ለእኔ ያቀድከው ሃሳብ አለ
- የእኔ የህይወት እቅድና ንድፍ በአንተ ዘንድ አለ
- እኔ ለራሴ ከማውቀው በላይ አንተ ለእኔ ታውቃለህ
- አንተ ለእኔ ያለህ አላማ የፍቅር አላማ ነው
- አንተ ለእኔ የምታስበው ሃሳብ መልካም ብቻ ነው
በማለት ይህንን እግዚአብሄር ለህይወታችን ያለውን ሃሳብ ከእግዚአብሄር መፈለግና መከተል መንገዳችን እንዲቃና ያደርጋል፡፡
ምሳሌ 3፡6 በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ፥ እርሱም ጎዳናህን ያቀናልሃል።
የራስ ጥፋት
ለዲያብሎስም ፈንታ አትስጡት።
ይገርማል ፡፡ ሰይጣን በህይወታችን መግቢያ ካገኘ ስፍራ የሰጠነው እኛ ነን ማለት ነው፡፡ ምክኒያቱም እየሱስ በመስቀል ላይ ሲሰቀል የሰይጣንን ሃይልና ስልጣን ሁሉ ገፎታል፡፡
አለቅነትንና ሥልጣናትን ገፎ፥ ድል በመንሣት በእርሱ እያዞራቸው በግልጥ አሳያቸው። ቆላስይስ 2፡15
እርሱ ከጨለማ ሥልጣን አዳነን፥ ቤዛነቱንም እርሱንም የኃጢአትን ስርየት ወዳገኘንበት ወደ ፍቅሩ ልጅ መንግሥት አፈለሰን። ቆላስይስ 2፡13-14
ሰይጣን በህይወታችን ስፍራ የሚያገኘው እኛው ከሰጠነው ብቻ ነው፡፡ ከዚያ ውጭ በግድ ምንም ስፍራ ሊወስድ አይችልም፡፡
ሰይጣን በምድር ላይ ለእግዚአብሄር እየኖርን የእግዚአብሄርን ስራ እንድንሰራ በፍፁም አይፈልግም፡፡ ቢችል ከምድረ ገፅ ያጠፋናል፡፡ እኛ የምንኖረው በሰይጣን ምህረት አይደለም ፡፡ ሰይጣን ስለፈቀደልንና አስኮናኞች ኑሩ ብሎ ስለተወን አይደለም የምንኖረው ፡፡ ለእግዚአብሄር የምንኖረውና እግዚአብሄርን የምናገለግለው በሃይልና በስልጣን ነው፡፡
ግን ደግሞ ከፈቀድንለት እንደፈቀድንለት መጠን ሊሰርቅ ሊያርድና ሊያጠፋ ወደህይወታችን ይመጣል፡፡ ዮሃንስ 10፡10
ግን ለሰይጣን ስፍራ መስጠት ማለት ምን ማለት ነው?
ለሰይጣን ስፍራን መስጠት ልብን በንፅህና አለመጠበቅ ነው፡፡
ሰው በቁጣው ላይ ፀሃይ ሲገባና ምሬት ውስጥ ሲገባ ያ በህይወቱ ለሰይጣን በርን ይከፍታል፡፡ ሰይጣን በሰዎች ህይወት የሚሰራው ጥላቻን በህይወታቸው ሲያገኝ ብቻ ነው፡፡ ይጣን በሰዎች ህይወት የሚሰራው ሰዎች ፍቅርን ጥለው በራስ ወዳድነት ሲኖሩ ብቻ ነው፡፡
ቆሻሻ ዝንብን እንደሚጠራ ሁሉ ጥላቻና ራስ ወዳድነት ሰይጣንን ይጠራል፡፡ ጥላቻና ፍቅር ማጣት ለሰይጣን መራቢያ ለም መሬቱ ነው፡፡ ምሬትንና ጥላቻን ከህይወታችን ካስወገድን በህይወታችን ለሰይጣን ስፍራን እንከለክለዋለ፡፡
ተቆጡ ኃጢአትንም አታድርጉ፤ በቁጣችሁ ላይ ፀሐይ አይግባ፥ ለዲያብሎስም ፈንታ አትስጡት። ኤፌሶን 4፡26-27
በሃይማኖት ብትኖሩ
ብዙ ጊዜ እውነት በሃይማኖት ነኝ ብለን እንጠይቃለን፡፡ በህይወት ዘመን ሊመለስ የሚገባው ወሳኝ ጥያቄ ነው፡፡ ብዙ ጥያቄዎችን መመለስ እንኳን ባንችል ይህን በሃይማኖት ነኝን የሚለው ጥያቄ ከመለስን ይበቃል፡፡
በሃይማኖት መኖራችን ዘላለማችንን የት እንደምናሳልፍ ይወስነዋል፡፡ በሃይማኖት ብንኖር ለዘላለም ከእግዚአብሄር ጋር እንኖራልን፡፡ በሃይማኖት ካልኖርን ለዘላለም ከእግዚአብሄር ተለይተን ለሰይጣንንና ለመላእክቱ በተዘጋጀው እሳት ባህር ውስጥ እንጣላለን፡፡
ግን በሃይማኖት መሆናችን እንዴት ይታወቃል? በሃይማኖት ለመኖር ምንድ ነው ብቁ የሚያደርገን? እግዚአብሄርን ለማስደሰት ብቃትን የሚሰጠን ምንድነው ?
የማናችንም አስተያየት እዚህ ጋር አይሰራም፡፡ መፅሃፍ ቅዱስ ለዚህ መልስ አለው፡፡
በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ፤ ራሳችሁን ፈትኑ፤ ወይስ ምናልባት የማትበቁ ባትሆኑ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ በእናንተ ውስጥ እንዳለ ስለ እናንተ አታውቁምን? 2ኛ ቆሮንቶስ ሰዎች 13፡5
እየሱስ ስለሃጢያቴ ሞቷል በሶስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ ተነስቷል ብሎ የሚያምንና እየሱስ ጌታ እንደሆነ የሚመሰክር ሰው እግዚአብሄር ይቀበለዋል፡፡ እየሱስም በውስጡ መኖር ይጀምራል፡፡
ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤ ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና። ሮሜ 10፡9-10
ብቁ የሚያደርገን የራሳችን መልካም ስራ ሳይሆን እየሱስ ስለሃጢያታችን በመስቀል ላይ የከፈለውን ዋጋ ለእኔ ነው እየሱስ የሞተው በእኔ ምትክ ነው ብለን እየሱስን ወደልባችን መቀበላችን ነው፡፡ ብቃታችን እየሱስ በልባችን በውስጣችን መኖሩ ነው፡፡
በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ፤ ራሳችሁን ፈትኑ፤ ወይስ ምናልባት የማትበቁ ባትሆኑ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ በእናንተ ውስጥ እንዳለ ስለ እናንተ አታውቁምን? 2ኛ ቆሮንቶስ ሰዎች 13፡5
ፈጣን ባለጠግነት
የታመነ ሰው እጅግ ይባረካል ባለጠጋ ለመሆን የሚቸኵል ግን ሳይቀጣ አይቀርም። ምሳሌ 28፡20
እግዚአብሄር የራሱ እርምጃና ፍጥነት አለው፡፡ነገር ግን እግዚአብሄር በአንዴ አያሳድግም፡፡
በችኰላ የምትከማች ሀብት ትጐድላለች ጥቂት በጥቂት የተከማቸች ግን ትበዛለች። ምሳሌ 13፡11
የሚያስፈልጋችሁን
እንግዲህ። ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤ ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። ማቴዎስ 6፡31-32
እግዚአብሄር የሚያዘጋጀው የሚያስፈልገንን ነው፡፡ በሚያስገልገን መጠን ነው እግዚአብሄር የሚያቀርበው፡፡
እግዚአብሄር ተረፍ አድርጎ ካቀረበና አሁን ከሚያስፈልገን በላይ ከሰጠን እንኳን ያ ማለት ሌላ የሚያስፈልገን ነገር እየመጣ ነው ማለት ነው፡፡
ተረፍ ብሎ ካልመጣ ደግሞ እግዚአብሄር ይመስገን ፍላጎት የለብንም ማለት ነው፡፡
እግዚአብሄር የሚያቀርበው እንደ ፍላጎታችን መጠን እንጂ እንደ ጎረቤታችንም አይደለም፡፡ የእኛና የጎረቤታችን ፍላጎት ይለያያል፡፡ እግዚአብሄር ለእኛና ለጎረቤታቸን እኩል አያቀርብም፡፡
የእኛ አቅርቦት ከጎረቤታችን ከበለጠ ያ ማለት ይበልጥ ፍላጎት እየመጣብን ነው ማለት ነው፡፡ የጎረቤታችን ከእኛ ከበለጠ ደግሞ ጎረቤታችን የሚያስፈልገው ሁኔታ ላይ ነው ማለት ነው፡፡
ፅድቁንና መንግስቱን ስንፈልግ ምን እንደሚያስፈልገን የሚያውቅና የሚሰጥ አባት ማግኘትን የመሰለ ነገር የለም፡፡
የማይታይ እጅ
አንዳንድ ነገሮች በህይወታችን እንዲሆኑ እንጥራለን የአቅማችንን ሁሉ እናደርጋለን እንሞክራለን፡፡ አንዳንድ ነገሮች ይሆናሉ፡፡ ምንም ያህል ብንጥርና ብንለፋም አንዳንድ ነገሮች አይሆኑም፡፡ አንዳንዴ ደግሞ ይሆናልም ብለን ብዙም ልባችንን ያልጣልንበት ነገር ሲሆን ሲሰካካ እንመለከታለን፡፡
ስለ እግዚአብሄር አሰራር የማይረዳ ሰው ይህን እድሌ ነው ይላል፡፡ እኛ ግን እግዚአብሄር ነው እንላለን፡፡
በሰው ልብ ብዙ አሳብ አለ፤ የእግዚአብሔር ምክር ግን እርሱ ይጸናል። ምሳሌ 19፡21
እግዚአብሄር እኛን ሁላችንን ፈጥሮናል፡፡ እግዚአብሄር ለህይወታችን የሚፈልገው ነገር አለ፡፡ እኛ ለህይወታችን የማንፈልገው ነገር እንዳለ ሁሉ ደግሞ እግዚአብሄርም ለህይወታችን የማይፈልገው ነገር አለ፡፡ ይህንን ምክሩን ለማስፈፀም እግዚአብሄር ምድርንና ሰማይን በሚገባ እየተቆጣጠረ እየመራ ነው ፡፡
ሰው በራሱ በልቡ ያለውን ነገር ሁሉ ቢያደርግ አለም ምን ልትሆን እንደምትችል መገመትም ያስቸግራል፡፡
በሰው ልብ ብዙ ሃሳብ ቢኖርም መጨረሻ ላይ የሚያይለውና የሚበረታውና የሚፈፀመውም የእግዚአብሄር ሃሳብ ነው፡፡
ይህን ማወቅ እንዴት ያሳርፋል፡፡ ምንም እንኳን በሰው ልብ ውስጥ ያለው ሃሳብ ብዙ ቢሆንም ግን በርትታ የምትወጣውና የምትፈፀመው የመልካሙ የአባታችን የእግዚአብሄር ሃሳብ መሆኑን ማወቅ እጅግ ደስ ያሰኛል፡፡
ይህንኑ ሃሳብ በብሉይ ኪዳን ቋንቋ እንዲህ በማለት ሰባኪው ይገልፀዋል ፡፡
እኔም ተመለስሁ፥ ከፀሐይ በታችም ሩጫ ለፈጣኖች፥ ሰልፍም ለኃያላን፥ እንጀራም ለጠቢባን፥ ባለጠግነትም ለአስተዋዮች፥ ሞገስም ለአዋቂዎች እንዳልሆነ አየሁ፤ ጊዜና እድል ግን ሁሉን ይገናኛቸዋል። መክብብ 9፡11
ይገርማል እግዚአብሄር አይሆንም ካለ የሩጫ ድል ለፈጣን አይሆንም፡፡
እግዚአብሄር ካልሰጠ ባለጠግነት በቅልጥፍና አይመጣም፡፡
እግዚአብሄር ይሁን ካላለ ሰው አዋቂነቱ ብቻ ሞገስን አይሰጠውም፡፡
ሁሉን የሚሰካካው የሚያገናኘው የጊዜና የእድል ባለቤቱ እግዚአብሄር ራሱ ነው፡፡
በሰው ልብ ብዙ አሳብ አለ፤ የእግዚአብሔር ምክር ግን እርሱ ይጸናል። ምሳሌ 19፡21