Category Archives: Deligence

ድህነትህ እንደ ወንበዴ፥ ችጋርህም ሰይፍ እንደ ታጠቀ ሰው

deligence 11.jpgበታካች ሰው እርሻ፥ አእምሮ በጐደለውም ሰው ወይን ቦታ አለፍሁ። እነሆም፥ ሁሉ እሾህ ሞልቶበታል፥ ፊቱንም ሳማ ሸፍኖታል፥ የድንጋዩም ቅጥር ፈርሶአል። ተመለከትሁና አሰብሁ፤ አየሁትና ተግሣጽን ተቀበልሁ። ጥቂት ትተኛለህ፥ ጥቂትም ታንቀላፋለህ፥ ትተኛም ዘንድ ጥቂት እጅህን ታጥፋለህ፤ እንግዲህ ድህነትህ እንደ ወንበዴ፥ ችጋርህም ሰይፍ እንደ ታጠቀ ሰው ይመጣብሃል። ምሳሌ 24፡30-33

በአለም ላይ ለሁላችንም የሚበቃ ሃብት አለ፡፡ በአለም ውስጥ እጅግ ብዙ የተጠራቀመ ሃብት አለ፡፡ በአለም ውስጥ ብዙ ሲሳይ አለ፡፡

በድሆች እርሻ ላይ ብዙ ሲሳይ አለ፤ ምሳሌ 13፡23

አለም አገልግሎትንም የተጠማች ነች፡፡ አለም የሚያገለግላት ካገኘት ለመክፈል የተዘጋጀች ነች፡፡ አለም የማትፈልገው ሳያገለግሏት መጠቀም የሚፈልጉትን ነው፡፡ አለም የማትፈልገው በሚሰጡት አገልግሎት ላይ ሳይሆን በሚያገኘኙት ጥቅም ላይ የሚያተኩሩትን ሰዎች ነው፡፡ አለም የማትፈልገው ለማገልገል ሳይሆን ለመጠቀም የሚጋደሉትን ሰነፎችን ነው፡፡

የታካች ሰው ነፍስ ትመኛለች፤ አንዳችም አታገኝም፤ የትጉ ነፍስ ግን ትጠግባለች። ምሳሌ 13፡4

ካልሰራህ ካልተጋህ ድህነት ወደቤትህ እና ወደኑሮህ ለመግባት አይደራደርም፡፡ ድህነት የሰነፍ ሰው ህይወት ውስጥ ለመግባት ፈቃድ አይጠይቅም፡፡ ድህነት የሚመጣው እንደ ወንበዴ በግድ ነው፡፡ ትንሽ መዘናጋት ትንሽ በስራ ጊዜ ማረፍ ድህነትን ይጠራዋል፡፡

አንተ ታካች፥ ወደ ገብረ ጕንዳን ሂድ፥ መንገድዋንም ተመልክተህ ጠቢብ ሁን። አለቃና አዛዥ ገዢም ሳይኖራት፤ መብልዋን በበጋ ታሰናዳለች፥ መኖዋንም በመከር ትሰበስባለች። አንተ ታካች፥ እስከ መቼ ትተኛለህ? ከእንቅልፍህስ መቼ ትነሣለህ? ጥቂት ትተኛለህ፥ ጥቂት ታንቀላፋለህ፥ ትተኛም ዘንድ ጥቂት እጅህን ታጥፋለህ፤ እንግዲህ ድህነትህ እንደ ወንበዴ፥ ችጋርህም ሰይፍ እንደ ታጠቀ ሰው ይመጣብሃል። ምሳሌ 6፡6-11

ሰነፍ ሰው የማይሰራ ሰው ብቻ አይደለም፡፡ ሰነግፍ ሰው ስራውን እውቆ የማይሰራ ሰው ነው፡፡ ሰነፍ ሰው ሁሌ ቀስቃሽ የሚፈልግ ሰው ነው፡፡ ሰነፍ ሰው ሁሌ አበረታች የሚፈልግ ሰው ነው፡፡ ሰነፍ ሰው በራሱ ለመስራርት ለመትጋት መንሳሳት የሜለው ሰው ነው፡፡ ትጉህ ሰው የሚሰራ ብቻ አይደለም ትጉህ ሰው ነገሮችን በራሱ አነሳሽነት የሚይሰራ ሰው ነው፡፡ ትጉህ ሰው ለመስራት የሰውን ጉትጎታ የማይፈልግ ሰው ነው፡፡ ትጉህ ሰው ሸክም ያለው ሰው ነው፡፡ ትጉህ ሰው ሸክሙ የማያስተኛው ሰው ነው፡፡ ሰነፍ ሰው ገብረጉንዳን በራሱ አነሳሽነት የሚያስፈልገውን ሁሉ በትጋት ይሰራል፡፡

አለም ትጉህን ሰው ታከብራለች፡፡ አለም ሰነፍን አታከብርም፡፡ አለም ለትጉህ ሰው ቦታ አላት፡፡ አለም ሰነፍን ሰው ጥላ ነው የምትሄደው፡፡ አለም ሰነፍን ትንቃለች፡፡

በሥራው የቀጠፈ ሰውን አይተሃልን? በነገሥታት ፊት ይቆማል፤ በተዋረዱም ሰዎች ፊት አይቆምም። ምሳሌ 22፡29

ሰነፍ ሰው ከመጥቀም ይልቅ የላከውን ሰው ያማርራል ይጎዳል፡፡

ሆምጣጤ ጥርስን፥ ጢስም ዓይንን እንደሚጐዳ፥ እንዲሁም ታካች ለላኩት። ምሳሌ 10፡26

እንዲሁ በመቄዶንያ ሁሉ ላሉት ወንድሞች ሁሉ ታደርጋላችሁና። ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ከፊት ይልቅ ልትበዙ፥ በጸጥታም ትኖሩ ዘንድ ልትቀኑ፥ የራሳችሁንም ጉዳይ ልትጠነቀቁ፥ እንዳዘዝናችሁም፥ በውጭ ባሉት ዘንድ በአገባብ እንድትመላለሱ፥ አንዳችም እንዳያስፈልጋችሁ በእጃችሁ ልትሠሩ እንለምናችኋለን። 1ኛ ተሰሎንቄ 4፡10-12

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ትጋት #ስራ #መድከም #ጕንዳን #ሸክም #ጥሪ #አላማ #ግብ #መሪ #ፀጋ #የሚያስችልሃይል #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ  #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ትህትና #ልብ #እምነት

ለሰው የከበረ ሀብት ትጋት

deligence.jpgሰው የተሰራው በእግዚአብሄር በማረፍ እንዲሰራ ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው መጀመሪያ እንዲያርፍ ከዚያም እንዲተጋ ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው በእረፍት እንዲሰራ እንዲተጋ ነው፡፡

አንተ በምትሄድበት በሲኦል ሥራና አሳብ እውቀትና ጥበብ አይገኙምና እጅህ ለማድረግ የምታገኘውን ሁሉ እንደ ኃይልህ አድርግ። መክብብ 9፡10

የጉልበት ማጠራቀሚያ የለውም፡፡ ጉልበታችንን ባንጠቀምበት አይጠራቀምም፡፡ ጉልበታችንን ካልተጠቀምነበት እየበዛ ሳይሆን እያነሰ ነው የሚሄደው፡፡

ትንሽ ሰርቶ ትንሽ ከመኖር ብዙ ሰርቶ ብዙ መኖር ይሻላል፡፡ ትንሽ ሰርቶ ጉልበትን ጊዜንና አቅምን ከመፍጀት በደንብ መስራት በደንብ መኖር ይሻላል፡፡ በትንሽ ሰርቶ በትንሽ ከመኖር በደንብ ሰርቶ በደንብ መኖር ይሻላል፡፡

የታካች እጅ ችግረኛ ታደርጋለች፤ የትጉ እጅ ግን ባለጠጋ ታደርጋለች። ምሳሌ 10፡4

በአለም ላይ ትልቅ አቅም አለ፡፡ በከርሰ ምድር ውስጥ ብዙ ሃብት አለ፡፡ ለሰው ልጆች ሁሉ የሚበቃ ሃብት በምድር ውስጥ አለ፡፡ ነገር ግን ትጋትን ካላሳየን በስተቀር ያንን ሃብት ማግኘት አንችልም፡፡

አለም የሃብት ችግር ኖሮባት አታውቅም፡፡ አለም የትጋት እና የታማኝነት ችግር እንጂ የሃብት ችግር የለባትም፡፡ በአለም ላይ ለአለም ህዝብ ሁሉ የሚበቃ ብዙ አንጡረ ሃብት አለ፡፡ አለም በሃብት የተሞላች ነች፡፡ ያንን ሃብት ግን ማውጣት የሚችለው ትጉህ ሰው ብቻ ነው፡፡ ሰነፍ ሃብቱ አጠገቡ እያለ ሳያየው ሳይጠቀምበት በችግር ይሞታል፡፡

ታካች ሰው አደን ምንም አያድንም፤ ለሰው የከበረ ሀብት ትጋት ነው። ምሳሌ 12፡27

አለም አገልግሎትን የተጠማች ነች፡፡ የሚያገለግላት ሰው ከተገኘ አለም ማንኛውንም ዋጋ ለመክፈል ፈቃደኛ ነች፡፡ አለም የመክፈል ችግር የለባትም፡፡ አለም የማትፈልገው ሳይተጋ ሳይለፋ መጠቀም ብቻ የሚፈልገውን ሰው ነው፡፡ አለም ሳይሰራ ሳያገለግል ሳይለፋ የሚገለገልባትን ሰው አትፈልግም፡፡ አለም የምትፈልገው በታማኝነት የሚያገለግላትን ሰው ነው፡፡ በታማኝነት የሚያገለግላት ትጉህ ሰው ካገኘች አለም የሚያስፈልገውን ትከፍላለች፡፡

አንተ በምትሄድበት በሲኦል ሥራና አሳብ እውቀትና ጥበብ አይገኙምና እጅህ ለማድረግ የምታገኘውን ሁሉ እንደ ኃይልህ አድርግ። መክብብ 9፡10

ለመስራት ለመድከም ምድር ወርቃማ እድል አዘጋጅታለች፡፡ ሰው ሲሞት በመቃብር ይህንን የመስራት የመትጋት የማገልገል አድል ያገኘውም፡፡ ይህ እድል በምድር ላይ ላሉ ሰዎች ብቻ የተሰጠ እድል ነው፡፡

ደከመኝ ሰለቸኝ ሳንል ጉልበታችን አንጠፍጥፈን የሰው ልጆችን እንድናገለግል ተጠርተናል፡፡

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #ትጋት #ስራ #መድከም #መሪ #ፀጋ #የሚያስችልሃይል #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ  #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ትህትና #ልብ #እምነት