የአእምሮ ገዳም

1024px-Tatev_Monastery_from_a_distanceየእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ። ሮሜ 12፡2

ሰዎች እግዚአብሄርን በመፈለጋቸውና ከዚህ አለም ነፃ ለመውጣት በመፈለጋቸው ከአለም መሸሽና ገዳም መግባት ይፈልጋሉ፡፡ ይህንንም ለማድረግ ገዳም ቢገቡም ጠልተውት የመጡት ክፉ የሃጢያት ሃሳብ ተከትሎዋቸው ይመጣል፡፡ በዚህም ምክኒያት ምንም ከከተማ ወጥተው ገዳም ቢገቡም የአለማዊነት አስተሳሰብ በአእምሮአቸው እስካለ ድረስ ከአለም መለየት ያቅታቸዋል፡፡

መፅሃፍ ቅዱስ አለምን ስለማንመስልበት ገዳም ይናገራል፡፡ ይህን አለም አለመምሰል የምንችለው ብቸኛው መንገድ አእምሮዋችን በእግዚአብሄር ቃል ሲታደስና የአለም ክፉ አስተሳሰብ በልባችን ቦታ ሳያገኝ ሲቀር ብቻ ነው ፡፡

አለማዊ የሚያደርገን ከተማ መኖራችን ወይም ከሰው ተለይተን አለመኖራችን ሳይሆን አእምሮዋችን በእግዚአብሄር ቃል አለመታደሱና ከሃጢያት ሃሳብ ጋር መኖራችን ነው፡፡ አእምሮዋችን በእግዚአብሄር ቃል ሲቃኝና ሲለወጥ በህይወታችን ለአለማዊነት ምንም ስፍራ አይኖርም፡፡

አለማዊ ከሚያደርገን ከሃጢያት ሃሳብ ጋር እስካለን ድረስ ከከተማ ወጥተን ከሰው ተለይተን ገዳምም ብንገባ ከሃጢያት ባርነት አናመልጥም፡፡ ምክኒያቱም አለማዊ ከሚያደርገን የሃጢያት ክፉ ሃሳብ አእምሮዋችን እስካልታደሰ ድረስ አለምን አለመምሰል አንችልም፡፡

ነገር ግን ባለንበት በስራችን በምንኖርበት ቦታ ሁሉ በእግዚአብሄር ቃል አእምሮአችንን ካደስነው ይህን አለም ሳንመስል እግዚአብሄርን እያስደሰትን መኖርና ማገልገል እንችላለን፡፡

ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር  share ያድርጉ!

ለተጨማሪ ፅሁፎች

ማኅፀን ገብቶ ይወለድ?

የህይወት ጥያቄ

ይቻላል – እግዚአብሄርን ማስደሰት

 

 

 

About apostle AbiyWakumaDinsa

The fear of the Lord is the beginning of knowledge, but fools[a] despise wisdom and instruction. Proverbs 1:7 The fear of the Lord is the beginning of wisdom, and knowledge of the Holy One is understanding. Proverbs 9:10

Posted on July 21, 2016, in Faith, From The Heart, Heart Matters, Leadership, purpose, Uncategorized, Wisdom. Bookmark the permalink. 1 Comment.

Leave a comment