የተቀበልኸውን አገልግሎት እንድትፈጽሙው ተጠንቀቅ

church leader.jpg

የተቀበልኸውን አገልግሎት እንድትፈጽሙው ተጠንቀቅ

ለአክሪጳም፦ በጌታ የተቀበልኸውን አገልግሎት እንድትፈጽሙው ተጠንቀቅ በሉልኝ። ወደ ቆላስይስ ሰዎች 4፡17

ለአክሪጳም፦ በጌታ የተቀበልኸውን አገልግሎት እንድትፈጽሙው ተጠንቀቅ በሉልኝ ያለበት ምክኒያት አለው፡፡ በህይወቱና በአገልግሎቱ ብዙ ሰዎች አገልግሎታቸውን መፈፀም ሲያቅታቸው ተመልክቷል፡፡ ተጠንቀቅ ያለበት ምክኒያት ማንም ሰው ካልተጠነቀቀ አገልግሎትን ከመፈፀም ሩጫ ሊያቋርጥ እንደሚችል ስለሚረዳ ነው፡፡

ዴማስ የአሁኑን ዓለም ወዶ ትቶኛልና፥ ወደ ተሰሎንቄም ሄዶአል፤ ቄርቂስም ወደ ገላትያ ቲቶም ወደ ድልማጥያ ሄደዋል፤ 2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 4፡10

አገልግሎት ካለጥንቃቄ የሚፈፅሙት ቀላል ተልእኮ አይደለም፡፡ አገልግሎት ብርቱ ጥንቃቄን ይጠይቃል፡፡ በክርስትና ህይወትና አገልግሎት በተለያየ ምክንያት ወደኋላ መመለስ አለ፡፡

ከክርስትና ህይወትና አገልግሎትን በመንፈስ በመጀመር በስጋ ሊጨረስ የሚችልበት እድል ያለበት ጥንቃቄን የሚፈልግ አገልግሎት ነው፡፡

እንዲህን የማታስተውሉ ናችሁ? በመንፈስ ጀምራችሁ አሁን በሥጋ ትፈጽማላችሁን? ወደ ገላትያ ሰዎች 3፡3

ክርስትና ህይወትና አገልግሎት ጠላት የሚጠላውና በቀጣይነት የሚዋጋው አገልጋዩን ሊውጥ የተዘጋጀበት ልዩ ጥንቃቄን የሙፈግ አገልግሎት ነው፡፡

በመጠን ኑሩ ንቁም፥ ባላጋራችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አንበሳ ይዞራልና፤ 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 5፡8

ለአክሪጳም፦ በጌታ የተቀበልኸውን አገልግሎት እንድትፈጽሙው ተጠንቀቅ በሉልኝ። ወደ ቆላስይስ ሰዎች 4፡17

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ክርስቶስ #ጌታ #አገልግሎት #ጥንቃቄ #እምነት #እውቀት #መደገፍ #መፈፀም #በመንፈሴ #በሃይል #በብርታት #ፀጥታ #መመለስ #ማረፍ #ፅድቁን #ኢየሱስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ፀጥታ #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #መታመን #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

About apostle AbiyWakumaDinsa

The fear of the Lord is the beginning of knowledge, but fools[a] despise wisdom and instruction. Proverbs 1:7 The fear of the Lord is the beginning of wisdom, and knowledge of the Holy One is understanding. Proverbs 9:10

Posted on June 21, 2018, in ministry. Bookmark the permalink. Comments Off on የተቀበልኸውን አገልግሎት እንድትፈጽሙው ተጠንቀቅ.

Comments are closed.