እኔም እመልስልሃለሁ ይላል እግዚአብሔር

%e1%8a%90%e1%8a%92%e1%8c%88%e1%88%80%e1%89%b0ወደ እኔ ጩኽ፥ እኔም እመልስልሃለሁ፤ አንተም የማታውቀውን ታላቅና ኃይለኛ ነገርን አሳይሃለሁ። ኤርምያስ 33፡3
እግዚአብሄር እንዲህ ይላል፡፡ ወደ እኔ ጩኽ!
እግዚአብሄርን የማንፈልግበት የህይወት ክፍል የለም፡፡ እግዚአብሄር የማያስፈልገን የህይወት ደቂቃና ሰከንድ የለም፡፡ እግዚአብሄር የማያስፈልገን ምንም የህይወት ሃላፊነት የለም፡፡ እግዚአብሄር የማያስፈልገን ምንም የህይወት ደረጃ የለም፡፡
ባደግን በተለወጥን ቁጥር ይበልጥ ወደ እርሱ መፀጮኽ እንዳለብን እንረዳለን፡፡ ባወቅንና በተረዳን ቁጥር ወደ እርሱ ጩኸን ፀልየን አንጠግብም፡፡ ብዙ የህይወት ደረጃዎች ላይ በደረስን መጠን እግዚአብሄርን የማንፈልግበት ዝርዝር ጥቃቅን የህይወት መስክ እንደሌለ እንረዳለን፡፡
የፀሎታችን ተጠቃሚ እንድንሆን እግዚአብሄርም ሁል ጊዜ የሚጠይቀን ወደ እርሱ እንድንጮኽ ነው፡፡ እግዚአብሄር ሁልጊዜ ከእኛ የሚጠብቀው የእኛን ወደ እርሱ አብዝተን መጮኻችንን ነው፡፡
አንተ የማታውቅውን ታላቅና ሃይለኛን ነገር አሳይሃለሁ፡፡
እንዴት አይነት የተስፋ ቃል ነው ?
አንተ የማታውቀውን ይላል እግዚአብሄር፡፡ ይገርማል፡፡
እግዚአብሄር ሲያስደንቀን ኖሮዋል፡፡ እግዚአብሄር የዘላለም አምላክ የምድር ዳርቻ ፈጣሪ ነው ማስተዋሉም አይመረመርም፡፡ ይህ እግዚአብሄር እንዲህ ይላል ወደ እኔ ጩኽ አንተ የማታውቀውን ነገር አሳይሃለሁ፡፡
እንደዚህ ልብን በደስታ ፈንጠዚያ የሚሞላ የተስፋ ቃል የለም፡፡
አንተ የማታውቀውን አዲስን ነገር እግዚአብሄር ሊያደርግ ወደ እርሱ እስከምትፀልይ እየጠበቀህ ነው፡፡ ታላቁ እግዚአብሄር እንዲህ ይላል ወደ እኔ ጩኽ እኔም እመልስልሃለሁ ፣ አንተም የማታውቅውን ታላቅን ነገር አሳይሃለሁ፡፡
ትንሽ ነገር አይደለም ታላቅ ነገር ተዘጋጅቶልሃል፡፡ ታላቅ ነገር ምን እንደሆነ መገመት ሊያቅትህ ሁሉ ይችላል፡፡ መገመት ቢያቅትህም እግዚአብሄር ግን እንዲህ ይላል ወደ እኔ ጩኽ፥ አንተም የማታውቀውን ታላቅ ነገር አሳይሃለሁ፡፡
እግዚአብሄር ሃያል አምላክ ነው፡፡ እግዚአብሄር የሰራዊት አምላክ ነው፡፡ እግዚአብሄር በሃይሉ ታላቅን ነገር ያደርጋል፡፡ ይህ እግዚአብሄር እንዲህ ይላል፡፡ ወደ እኔ ጩኽ፥ አንተም የማታውቀውን ታላቅና ኃይለኛ ነገርን አሳይሃለሁ።
ወደ እኔ ጩኽ፥ እኔም እመልስልሃለሁ፤ አንተም የማታውቀውን ታላቅና ኃይለኛ ነገርን አሳይሃለሁ። ኤርምያስ 33፡1-3
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #ፀሎት #ታላቅ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ትጋት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #ሃይለኛ #ጩኽ #በረከት #ትግስት #መሪ

About apostle AbiyWakumaDinsa

The fear of the Lord is the beginning of knowledge, but fools[a] despise wisdom and instruction. Proverbs 1:7 The fear of the Lord is the beginning of wisdom, and knowledge of the Holy One is understanding. Proverbs 9:10

Posted on October 26, 2016, in Prayer and tagged , , , , . Bookmark the permalink. Comments Off on እኔም እመልስልሃለሁ ይላል እግዚአብሔር.

Comments are closed.