መልካም ምግባር አይበቃም!

ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤ ሮሜ 3፡23
የዚህ የእግዚአብሄር ክብር የጎደለው ሰው መጨረሻ ለዘላለም ከእግዚአብሄ መለያየት ነው፡፡
የኃጢአት ደመወዝ ሞት ነውና፤ ሮሜ 6፡23
ይህንን ለዘላለም ከእግዚአብሄር በመለየት በሞት የሚያስፈርደውን ፍርድ ሊለውጥ የሚችል ማንም ነገር የለም፡፡ እግዚአብሄር ግን በምህረቱ ሃጢያት ያልሰራውን አንድ ልጁን በመስቀል ላይ እንዲሞት በማድርግ የሃጢያታችንን ዋጋ ከፈለ፡፡
አሁን ሰው እግዚአብሄር ያዘጋጀውንም ይህንን የመዳኛ መንገድ እየሱስን ከተቀበለና እየሱስ ከሙታን እንደተነሳ በልቡ ካመነ እንዲሁም እየሱስ ጌታ እንደሆነ በአፉ ከመሰከረ ይድናል፡፡
ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤ ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና። ሮሜ 10፡9-10
ምንም በሰራው መልካም ስራ ሳይሆን እግዚአብሄር ለመዳኛ የሚሆነውን የሃጢያትን እዳ የከፈለውን እየሱስን የተቀበለውን እግዚአብሄር ልጅ አድርጎ ይቀበለዋል፡፡
ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ዮሃንስ 1፡12
በመልካም ስራው ሳይሆን እየሱስን በማመን ብቻ የዳነው ሰው እግዚአብሄር ያዘጋጀለትን መልካመ ስራ በመስራት እግዚአብሄርን ያስደስተዋል፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
Advertisements
Posted on August 9, 2016, in salvation, Uncategorized. Bookmark the permalink. 3 Comments.
Pingback: መልካም ምግባር አይበቃም! — Talking from the heart Blog | Talking from the heart Blog
Pingback: አዋጅ ! | Talking from the heart Blog
Pingback: የምትሠሩልኝ ቤት ምን ዓይነት ነው? ይላል እግዚአብሄር | Talking from the heart Blog