እኛም ተነስተናል
ትንሳኤ ለተለያዩ ሰዎች የተለያየ ትርጉም አለው፡፡ ብዙ ሰዎች የትንሳኤን ትርጉምና ከእኛ ህይወት ጋር ያለውን ተዛምዶ በፍፁም አይረዱትም፡፡ በዚያም ምክኒያት የትንሳኤን ሙሉ ጥቅም በህይወታቸው ተጠቃሚ መሆን አይችሉም፡፡
ለአንዳንዶች የአመት አንድ ቀን ብቻ ነው፡፡ ለሌሎች ደግሞ እየሱስ ስለሃጢያታችን ይቅርታ ከሙታን የተነሳበት ቀን ነው፡፡
የትንሳኤው አላማ ይህንን የሚያጠቃልልም ቢሆንም ከዚህ ሁሉ ግን ያለፈ ትርጉም አለው፡፡ እየሱስ በመስቀል የሞተውና በሶስተኛ ቀን ሞትን ድል አድርጎ የተነሳው የሃጢያታችንን ዋጋ ለመክፈል ብቻ ሳይሆን ከዚያም በኋላ ከሃጢያት በላይ ሆነን እንድንኖር ይህን የሃጢያት ስጋችንን በመስቀል ላይ ለመስቀልና ለመግደል ነው፡፡
እየሱስ በመስቀል ላይ ሲሞትና ሲነሳ እኛም ለሃጢያት ሞተን ለእግዚአበሄር ፅድቅ ህያዋን እንድንሆን ራሳችነነ በእምነት እንድናስተባብር ነው፡፡
እየሱስ በመስቀል ላይ ያደረጋቸው ነገሮች ሁሉ ያደረገው ለራሱ አልነበረም፡፡ እየሱስ በመስቀል ላይ የሞተውና የተነሳው ለእኛ ነው፡፡ እየሱስ ይህንን ሁሉ ያደረገው እኛን ተክቶ ነው፡፡ እየሱስ ሲሞትና ሲነሳ የእኛን ታሪክ እየሰራው መሆኑን ማወቅ አለብን፡፡
እየሱስ ሲሞት የሞትኩት እኔ ነኝ ብለን መውሰድ እየሱስ ሲነሳ እኔም ከእርሱ ጋር ተነስቻለሁ ብለን መውሰድ እንችላለን፡፡
እየሱስ በመስቀል ላይ ሲሞት የእኛ የሃጢያት…
View original post 204 more words
Posted on April 28, 2016, in Uncategorized. Bookmark the permalink. Leave a comment.
Leave a comment
Comments 0